07/07/2022
"…የድረሱልን ጥሪ ከወለጋ…!!
"…የዛሬ ሳምንት የወረዳው አስተዳዳሪ "ማንን ልትመቱበት ነው መሳሪያ የታጠቃችሁት? በማለት የኦሮሚያ ልዩ ኃይልን ልኮ ከሚኒሻዎቹም ከህዝቡም ላይ ሰብስቦ አስወሰደ። ይኸው በሳምንቱ ዛሬ አንድ መኪና ሙሉ ሸኔ በከተማችን ላይ መጥቶ ፈሰሰ።
"…ቦታው ምሥራቅ ወለጋ አንገር ጉትን የምትባል ከተማ እንደሆነች የድረሱልን ጥሪውን ያደረሱኝ ወገኖች ተናግረዋል። ለሚመለከተው አካል ብናመለክትም ምንም መልስ አላገኘንም። ጭራሽ ራሳችሁ ጠብቁ ነው እያሉ የሚሳለቁብን። ከባድ መሳሪያን የታጠቀ ቡድን እንዴት አድርገን ነው ባዶ እጃችንን እምንከላከለው? እናም መምህር ሆይ እባክህ እንደ ግጎረቤታችን ቄለም ወለጋ ሳንሆን ለሚመለከተዉ አካል ለፌደራል መንግሥቱ አመልክትልን። ይሄው አመለከትኩላቸው።
አሶሳ…!!
"…አሶሳም የተኩስ ድምጽ እየተሰማ ነው። የዛሬ ተረኛዋ አሶሳ ነበረች ብሎ ዐቢይ አሕመድ ጠዋት ፓርላማ ላይ መናገሩ ይታወሳል።
"…ፈጣሪ ይድረስላችሁ…!! ከመ /ር ዘመዴ የተወሠደ