01/10/2025
ነብስ ይማር ወገኖቻችን
በምንጃር ሸንኮራ የአረርቲ ማርያም ቤተክርስቲያን ግንባታ ርብራብ በመደርመሱ ከባድ አደጋ ደረሰ!
የሞትና የአካል ጉዳት አጋጠመ
ምንጃር ሸንኮራ፣ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን፣ ምንጃር ሸንኮራ ወረዳ ውስጥ በሚገኘው አረርቲ ማርያም ቤተክርስቲያን በደረሰ ከባድ አደጋ የበርካታ ሰዎች ህይወት ማለፉንና የአካል ጉዳት መድረሱን የወረዳው ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ አረጋግጧል።
የአደጋው መንስኤ፣ ለቤተክርስቲያኗ ፊኒሺንግ ሥራ ተብሎ ተረብርቦ የነበረ የእንጨት ግንባታ (ርብራብ) መደርመስ ነው።
የወረዳው ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ኑርላህ ከድር ለኢትዮ ኤፍ ኤም በሰጡት መረጃ፣ አደጋው የተከሰተው ቤተክርስቲያኗ ዓመታዊ የማርያም ክብረ በዓልን ምክንያት በማድረግ የንግስ ሥነ ሥርዓት እየተካሄደና ሰዎች የግንባታውን ሂደት እየጎበኙ በነበሩበት ወቅት ነው።
* ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ በርካታ ሰዎች ህይወታቸው ወዲያውኑ አልፏል።
* ርብራቡ የተጫናቸው ሌሎች ተጎጂዎችን ከፍርስራሽ ስር የማውጣቱ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገልጿል።
ይህ አሳዛኝ ክስተት የተፈጸመው መስከረም 21 ቀን 2018 ዓ.ም ነው።
©️ኢትዮ ኤፍ ኤም
💔💔💔