08/06/2026
በሀላባ ዞን በዌራ ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ፅ/ቤት 8.6 ኪ.ሜ መንገድ ግንባታ ሥራ ሕብረተሰቡን በማስተባበር ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው
=====
ሰኔ 01/2018 በዌራ ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ፅ/ቤት ህብረተሰቡን በማስተባበ አርሾ አቦክቾ-አርቶ-ምዕራብ ጎርጣንቾ ቀበሌ 8.6 ኪ.ሜ 100% መንገድ ግንባታ ሥራ ተጠናክሮ የቀጠለ ስሆን የመንገድ ያለበት ደረጀ በዛሬው ዕለት ምልከታ ተደርጓል።
በዞኑ የቱርስት መስህብ የሆነዉ ወዳ አርቶ ፍል ዉሃ የሚወስደዉን መንገድ ማለትም ከታች አርሾ - አቦክቾ - አርቶ -ምዕራብ ጎርጣንቾ 8.6 ኪ.ሜ 100% የመንገድ ግንባታ ስራ በፍጥናት እና በጥራት እየተሰራ ይገኛል።
መንገዶች የዉስጥ ለዉስጥ ጥገና ሥራ በጥሩ ሁኔታ እየተሰራ ስሆን ህብረተሰቡ ከልማቱ ጎን በመሠለፍ ድጋፍ እና ትብብር ማድረግ እንደሚገባ ተገልጸዋል።
በየደረጃው እየተሰሩ ያሉ የቀበሌ የውስጥ ለውስጥ የመንገድ ስራዎች መንደርን ከመንደር ቀበሌን ከቀበሌ የሚያገናኙ ስለመሆናቸው በምልከታው ወቅት ተጠቁሟል።
በየቀበሌው የሚስተዋሉትን የውስጥ ለውጥ የመንገድ ተደራሽነት ችግሮችን ለመቅረፍ ደረጃ በደረጃ ምላሽ ማግኘት እንዲችሉ በቅንጅት እና በትኩረት ይሰራል ተብሏል።
የመንገዱን ጥገናውን የዌራ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤ ምክትል እና የፖለቲካ እና አቅም ግንባታ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ጀማል አህመድ የዌራ ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ቹቹ መሀመድ ምልከታ መደረጋቸውን ከወረዳው መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
ቴሌግራም፦ https://t.me/+eIbzwXJYyQNlYjVk
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/profile.php?id=100083958027668
በቲክቶክበ፦ tiktok.com/
በቲውተር፦ https://x.com/Halabazonecomun?t=jrF0ELvPbOBJOuLT6X3G1A&s=09
ዋትስአፕ፦ https://whatsapp.com/channel/0029Vb3YNPxJZg4GKKQ3Om3v
ዩቲዩብ፦ https://youtube.com/?si=SJOXf764DKjW1CUe
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/halabazonecomunication?igsh=a3NwdTUwand6NWhn
ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን!!