አይከል ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ Aykel tvet collage

አይከል ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ Aykel tvet collage የሙያ ባለቤት መሆን ያስከብራል

ዜና እረፍት😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭13/12/2018 ዓ.ም :-አይከል:-በውድ የዳታ ቤዝ ኤክስቴንሽን ሰልጣኛችን  #ምህረት ደረጀ ድንገተኛ ህልፈት የአይከል ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ...
19/08/2026

ዜና እረፍት
😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭

13/12/2018 ዓ.ም :-አይከል:-በውድ የዳታ ቤዝ ኤክስቴንሽን ሰልጣኛችን #ምህረት ደረጀ ድንገተኛ ህልፈት የአይከል ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን እየገለፀ ፣ ለመላው ቤተሰብና ወዳጅ ዘመዶቹ መጽናናትን እንመኛለን።

ነፍሱን ይማረው፤ ለቤተሰቡ ፈጣሪ ብርታትና መጽናናት ይስጥ‼️😭😭😭

እውነት ነው ኮሌጆች ሊደገፉ ይገባል‼️
17/08/2026

እውነት ነው ኮሌጆች ሊደገፉ ይገባል‼️

ትምህርት ላይ መስራት ሀገር መገንባት ነው‼️
15/08/2026

ትምህርት ላይ መስራት ሀገር መገንባት ነው‼️

መልካም የስራ ዘመን ‼️
28/07/2026

መልካም የስራ ዘመን ‼️

25/07/2026
በአይከል ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ተካሄደ::አይከል፣ ሐምሌ- 14/2018 ዓ.ም – በአይከል ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ የአካባቢ ጥበቃን እና አረንጓዴ ልማ...
21/07/2026

በአይከል ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ተካሄደ::

አይከል፣ ሐምሌ- 14/2018 ዓ.ም – በአይከል ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ የአካባቢ ጥበቃን እና አረንጓዴ ልማትን ለማጠናከር ያለመ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ተካሂዷል።

በመርሃ-ግብሩ የኮሌጁ አመራሮች፣ መምህራን፣ ሠራተኞች እና ሰልጣኞች በንቃት ተሳትፈው በኮሌጁ ቅጥር ግቢ ውስጥ የተለያዩ የዛፍ ችግኞችን ተክለዋል።

የኮሌጁ አመራሮች እንደገለጹት፣ የችግኝ ተከላ ፕሮግራሙ የአካባቢ ጥበቃን ከማጠናከር ባሻገር የአፈር ልምነትን ሊያሳድጉ የሚችሉ የዛፍ አይነቶችን የተተከሉ መሆኑንና መትከል ብቻ ሳይሆን እንክብካቤንም ጭምር እንደባህል ለማጎልበት በቀጣይ መሰራት እንደሚጠይቅ ገልፀዋል።

በሶስት ዓመት ውስጥ ያገኛችሁትን እውቀት ወደ ተግባር በመቀየር ማህበረሰባችሁን በቅንነት አገልግሉ!አቶ ገብረመድን አለሙ – የአይከል ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ዲንሐምሌ 11/2018  ጭልጋ ኮሙኒኬ...
19/07/2026

በሶስት ዓመት ውስጥ ያገኛችሁትን እውቀት ወደ ተግባር በመቀየር ማህበረሰባችሁን በቅንነት አገልግሉ!

አቶ ገብረመድን አለሙ – የአይከል ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ዲን

ሐምሌ 11/2018 ጭልጋ ኮሙኒኬሽን

በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የአይከል ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ለ14ኛ ዙር በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ለሶስት ዓመታት ያሰለጠናቸውን 107 ተማሪዎች በደማቅ ሥነ-ሥርዓት አስመረቀ።

በምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የኮሌጁ ዲን አቶ ገብረመድን አለሙ ለተመራቂዎቹ ባስተላለፉት መልዕክት፣ በኮሌጁ ቆይታቸው ያገኙትን ዕውቀት፣ ክህሎትና ሙያዊ ብቃት በተግባር በመተርጎም ለራሳቸው፣ ለቤተሰባቸውና ለአገራቸው ጠቃሚ እንዲሆኑ አሳስበዋል።

ዲኑ አክለውም፣ ተመራቂዎቹ የተማሩትን ሙያ በሥነ-ምግባር፣ በታማኝነትና በቅንነት በመተግበር የማህበረሰቡን ፍላጎት ማሟላት፣ የሥራ ፈጣሪ መሆን እና ለሀገር ኢኮኖሚያዊ እድገት የሚገባውን አስተዋፅኦ ማበርከት እንደሚጠበቅባቸው ገልጸዋል።

አቶ ገብረመድን አለሙ፣ “በሶስት ዓመታት ውስጥ ያገኛችሁትን እውቀት ወደ ተግባር በመቀየር ማህበረሰባችሁን በቅንነት አገልግሉ፤ ሙያችሁ የእናንተ ብቻ ሳይሆን የሀገር እድገት መሠረት ነው” በማለት ለተመራቂዎቹ አደራ አስተላልፈዋል።

በመጨረሻም ኮሌጁ በቀጣይም የጥራት ያለው የቴክኒክና ሙያ ስልጠና በመስጠት ብቁ፣ ተወዳዳሪና ሥራ ፈጣሪ ዜጎችን ለማፍራት ቁርጠኛ መሆኑን ገልጿል።

መልካም ምርቃት! ለሁሉም ተመራቂዎች በቀጣይ ህይወታቸው የተሳካ ሙያዊ ጉዞ እንመኛለን።

የአይከል ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን ሰልጣኞች አስመርቋል ።አይከል : ሀምሌ 11/ 2018 ዓ/ም የአይከል ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅየአይከል ቴክኒ...
18/07/2026

የአይከል ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን ሰልጣኞች አስመርቋል ።

አይከል : ሀምሌ 11/ 2018 ዓ/ም የአይከል ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ

የአይከል ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 107 ሰልጣኞችን ለ14ኛ ጊዜ አስመርቋል።

በተማራችሁት ሙያ ሀገራችሁን በማገልገል የራሳችሁን እና የማህበረሰባችሁን እድገት እንደምታፋጥኑ እምነታችን ጽኑ ነው።

ለውድ ተመራቂዎቻችን እና ቤተሰቦቻችሁ እንኳን ደስ አላችሁ።

17/07/2026

Address

Amhara Region

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አይከል ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ Aykel tvet collage posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The University

Send a message to አይከል ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ Aykel tvet collage:

Shortcuts

Share