Debre work TVET college

Debre work TVET college Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Debre work TVET college, College & University, Debre work, Debre Werk'.

26/03/2022

አስደሳች ዜና ለስልጠና ፈላጊዎች በሙሉ!!
የደብረ ወርቅ ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ እንኳን ለ2014 ዓ.ም የስልጠና ዘመን በሰላም አደረሳችሁ እያለ !!
በዝቅተኛና በመካከለኛ ደረጃ የሰለጠኑ ብቁ ባለሙያዎችን ማፍራት ተልዕኮ ያደረገው የደብረ ወርቅ ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች በቀኑና በማታው መርሀ ግብር ስልጠና ይሰጣል፡፡
በመሆኑም በፈለጉት የሙያ ዘርፍ በመሰልጠን የሙያ ባለቤትና ስራ ፈጣሪ እንዲሆኑ ለማድረግ ኮሌጁ ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡
ከዚህ በፊት ስልጠና ከሚሰጥባቸው የስልጠና ዘርፎች በተጨማሪ አዳዲስ የሙያ መስኮችን በመክፈት ከአላስፈላጊ ወጪና እንግልት በመታደግ የሙያ ባለቤት ያደርገዎታል፡፡ ስለዚህ የዚህ እድል ተጠቃሚ ይሆኑ ዘንድ ምርጫዎ የደብረ ወርቅ ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ ይሁን፡፡

ስልጠና የምንሰጥባቸው የሙያ መስኮች፡-
1. Building Construction Sector
1.1 Masonry ደረጃ II
1.2 Bar bending And concrete work ደረጃ II
1.3 Onsite building construction ደረጃ IV
1.4 Building construction management ደረጃ V
1.5 Plumbing Installation ደረጃ II
1.6 Onsite plumpbing installation ደረጃ IV
1.7. Building electrical installation ደረጃ II
1.8. Onsite Building Electrical Installation ደረጃ IV
1.9. Building Electrical installation management ደረጃ V
2. Electro technology Sector
2.1 Basic Electronics Communication and Multimedia Equipment Servicing ደረጃ II
2.2 Electrical/Electronics Equipment Servicing Management ደረጃ IV
3 . Road Construction Sector
3.1 Road civil work ደረጃ II
3.2 Rigid & flexible road surfacing ደረጃ IV
4 Industry Development Sector
4.1 Furniture Making ደረጃ II እና IV
4.2 Welding ደረጃ II እና IV
4.3 Metal manufacturing management ደረጃ V
4.4 Intermediate Apparel Production ደረጃ II
4.5 Apparel Fashion Design And Supervision ደረጃ IV
4.6 Vehicle servicing & repairing ደረጃ II
4.7 Automotive electromechanical diagnosis ደረጃ IV
5 Agriculture Sector
5.1 Animal Production ደረጃ IV
5.2 Crop Production and Marketing management ደረጃ IV
ያለን ቦታ ውስን በመሆኑ ፈጥነው ይመዝገቡ!!!
ቀድሞ መገኘት ብልህነት ነው!!

የመግቢያ ነጥብ !!
12ኛ ክፍል በተፈጥሮ ሳይንስ ላጠናቀቁ
ለደረጃ 1 እና 2
ለወንዶች 209 እና ከዚያ በታች
ለሴቶች 204 እና ከዚያ በታች
ለደረጃ 3 እና 4
ለወንዶች 210 እና ከዚያ በላይ
ለሴቶች 205 እና ከዚያ በላይ
ለደረጃ 5
ለወንዶች 280 እና ከዚያ በላይ
ለሴቶች 275 እና ከዚያ በላይ

ለ12ኛ ክፍል በማህበራዊ ሳይንስ ላጠናቀቁ
ለደረጃ 1 እና 2
ለወንዶች 159 እና ከዚያ በታች
ለሴቶች 154 እና ከዚያ በታች
ለደረጃ 3 እና 4
ለወንዶች 160 እና ከዚያ በላይ
ለሴቶች 155 እና ከዚያ በላይ
ለደረጃ 5
ለወንዶች 235 እና ከዚያ በላይ
ለሴቶች 230 እና ከዚያ በላይ
ማሳሰቢያ፡-እያንዳንዱ ሰልጣኝ ወደ ኮሌጁ ለምዝገባ በሚመጣበት ጊዜ፤
-የ12ኛ ክፍል ኦርጅናል ካረድ ፣ትራንስክሪፕት እና የ8ኛ ክፍል ካርድ ከፎቶ ኮፒ ጋር እንዲሁም ክናሴር ለመመዝገቢያ 50/ሃምሳ ብር/ ብቻ በመያዝ ከመጋቢት 19/2014 ዓ.ም እስከ ከመጋቢት 232014 ዓ.ም ኮሌጁ ድረስ በመምጣት መመዝገብ የሚቻል መሆኑን እንገልፃለን!!
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር
 0586630234
 0912647474

04/10/2021

ብልኋ እንቁራሪት

አንዲት እንቁራሪት በኩሬ ውስጥ ያለች
የሚቃጠል መንደር ፥ ከሩቁ እያየች
ትፀልይ ጀመረ ፥ እንደዚህ እያለች
እባክህ ጌታዬ ይህን እሳት አጥፋው
ባለበት እንዲቆም ግዛቱን አታስፋው
ብላ ለፈጣሪ ፥ አዝና ስትናገር
ለካስ ካጠገቧ እባብ ቆሞ ነበር
እሱም በመገረም ፥ በጸሎቷ ነገር
የሽሙጥ እያየ እንዲህ ይላት ጀመር
እንደ ምን ትገርሚ እንደምን ትደንቂ
እሳቱ እንዲጠፋ ፥ ጌታን 'ምጠይቂ
እሱ 'ሚነድ እዛ እሩቅ ነው ካንቺ ዘንድ
በምን ደርሶብሽ ነው ያንቺን ቤት የሚያነድ ?
ደሞም ከውሃ ውስጥ ቁጭ ብለሽ ያለሽው
የማይደርስብሽን ፥ እሳት የምትፈሪው
እያለ በሹፈት ፥ ከልቡ ሳቀባት
ወደታች በንቀት አዘቅዝቆ እያያት
ይ'ን ጊዜ እቁራሪት እየተገረመች
በእባብ ጅልነት በጣም እያዘነች
እንዲ ትለው ጀመር ቀና ብላ እያየች
አዎ ትክክል ነህ ፥ እሳቱ እሩቅ ነው
እኔም ያለሁበት ዙሪያውን ውሀ ነው
ነገር ግን አስተውል እጅግ አትሳት
ቃጠሎውን ቶሎ ወዲያው ካላቆሙት
ከ'ኔ ዘንድ መ'ተው ነው ውሀ የሚቀዱት
እናም ያላወከው እውነታው ይሄ ነው
ምንም'ኳ እዚህ ብቀመጥ ከውሃው
እዛ እሩቅ ቢሆን መንደሩ 'ሚነደደው
ካልጠፋ በጊዜ ፥ አምላክ ካላቆመው
የ' ኔም ቤት ነውና ተዝቆ የሚያልቀው
ስለዚህ ወዳጄ አያጥቃህ ጅልነት
ቃጠሎው ባይደርስም እኔ ካልሁበት
እዛ ነዶ ነዶ ፥ እጅግ ከባሰበት
ባልዲ ተሸክመው ሲመጡ ለመቅዳት
ይከቱኛል ወስደው ፥ ከሚነደው እሳት
ይህን አውቄ ነው ከሩቁ መፍራቴ
አጥፋው በሚል ፀሎት ምድር መደፋቴ
የአቅሜን ያህል እነሱን መርዳቴ
ብላ ስትናገር ፥ እባብን ገረመው
ማየት ያልቻለውን ገልጣ ስታሳየው
እናም እሩቅ ያለ ከ' እኛ የማይደርስ
የሌላ ነው ያልነው ፥ እሳቱ ሲለኮስ
ስለማይቀር እዚ ፥ መምጣቱ ቀስ በቀስ
ትልቅ እገዛ ነው
የሰው ችግር አይቶ ፥ ለኔ ብሎ ማልቀስ

━━━━━━✦✗✦━━━━━━━
ምርጫዎ የደብረ ወርቅ ቴክኒክና ሙያ መሰልጠኛ ኮሌጅ ፔጅ ስለሆነ እናመሰግናለን

ከ ፍፁም ቃል

04/10/2021

አስደሳች ዜና ለስልጠና ፈላጊዎች በሙሉ!!
የደብረ ወርቅ ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ እንኳን ለ2014 ዓ.ም የስልጠና ዘመን በሰላም አደረሳችሁ እያለ !!
በዝቅተኛና በመካከለኛ ደረጃ የሰለጠኑ ብቁ ባለሙያዎችን ማፍራት ተልዕኮ ያደረገው የደብረ ወርቅ ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች በቀኑና በማታው መርሀ ግብር ስልጠና ይሰጣል፡፡
በመሆኑም በፈለጉት የሙያ ዘርፍ በመሰልጠን የሙያ ባለቤትና ስራ ፈጣሪ እንዲሆኑ ለማድረግ ኮሌጁ ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡
ከዚህ በፊት ስልጠና ከሚሰጥባቸው የስልጠና ዘርፎች በተጨማሪ አዳዲስ የሙያ መስኮችን በመክፈት ከአላስፈላጊ ወጪና እንግልት በመታደግ የሙያ ባለቤት ያደርገዎታል፡፡ ስለዚህ የዚህ እድል ተጠቃሚ ይሆኑ ዘንድ ምርጫዎ የደብረ ወርቅ ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ ይሁን፡፡

ስልጠና የምንሰጥባቸው የሙያ መስኮች፡-
1. Building Construction Sector
1.1 Masonry ደረጃ II
1.2 Bar bending And concrete work ደረጃ II
1.3 Onsite building construction ደረጃ IV
1.4 Building construction management ደረጃ V
1.5 Plumping Installation ደረጃ II
1.6 Onsite plumping installation ደረጃ IV
1.7. Building electrical installation ደረጃ II
1.8. Onsite Building Electrical Installation ደረጃ IV
1.9. Building Electrical installation management ደረጃ V
2. Electro technology Sector
2.1 Basic Electronics Communication and Multimedia Equipment Servicing ደረጃ II
2.2 Electrical/Electronics Equipment Servicing Management ደረጃ IV
3 . Road Construction Sector
3.1 Road civil work ደረጃ II
3.2 Rigid & flexible road surfacing ደረጃ IV
4 Industry Development Sector
4.1 Furniture Making ደረጃ II እና IV
4.2 Welding ደረጃ II እና IV
4.3 Metal manufacturing management ደረጃ V
4.4 Intermediate Apparel Production ደረጃ II
4.5 Apparel Fashion Design And Supervision ደረጃ IV
4.6 Vehicle servicing & repairing ደረጃ II
4.7 Automotive electromechanical diagnosis ደረጃ IV
5 Agriculture Sector
5.1 Animal Production and Marketing Management ደረጃ IV
5.2 Crop Production and Marketing management ደረጃ IV

የመግቢያ ነጥብ !!
10ኛ ክፍል ላጠናቀቁ፤
ለደረጃ 2
ለወንዶች 1.57 እና ከዚያ በታች
ለሴቶች 1.43 እና ከዚያ በታች
ለደረጃ 4
ለወንዶች 1.71 እና ከዚያ በላይ
ለሴቶች 1.57 እና ከዚያ በላይ

ለአካል ጉዳተኞች
ለደረጃ 2
ለሁሉም ፆታዎች 1.14 እና ከዚያ በታች
ለደረጃ 4
ለሁሉም ፆታዎች 1.29 እና ከዚያ በላይ

ለ12ኛ ክፍል ላጠናቀቁ
ለደረጃ 2
ለወንዶች 200 እና ከዚያ በታች
ለሴቶች 190 እና ከዚያ በታች
ለደረጃ 3 እና 4
ለወንዶች 201እና ከዚያ በላይ
ለሴቶች 191 እና ከዚያ በላይ
ለደረጃ 5
ለወንዶች 301እና ከዚያ በላይ
ለሴቶች 291 እና ከዚያ በላይ
ለአካል ጉዳተኞች
ለደረጃ 5
ለወንዶች 301እና ከዚያ በላይ
ለሴቶች 291 እና ከዚያ በላይ
ማሳሰቢያ፡-እያንዳንዱ ሰልጣኝ ወደ ኮሌጁ ለምዝገባ በሚመጣበት ጊዜ፤
-የ12ኛ ወይም የ10ኛ ክፍል ኦርጅናል ካረድ ፣ትራንስክሪፕት እና የ8ኛ ክፍል ካርድ ከፎቶ ኮፒ ጋር እንዲሁም ክናሴር ለመመዝገቢያ 50/ሃምሳ ብር/ ብቻ በመያዝ ከመሰከረም 24/2014 ዓ.ም እስከ መሰከረም 26/2014 ዓ.ም ኮሌጁ ድረስ በመምጣት መመዝገብ የሚቻል መሆኑን እንገልፃለን!!

ያለን ቦታ ውስን በመሆኑ ፈጥነው ይመዝገቡ!!!
ቀድሞ መገኘት ብልህነት ነው!!

02/12/2020
02/12/2020

ቀን 23/03/2013 ዓ.ም

ምዘና ለመውሰድ ለሞላችሁ በሙሉ፡/
ከላይ በርዕሱ ለመግለፅ እንደተሞከረው በታህሳስ ወር ምዘና ለመውሰድ መሙላታቸሁ ይታወቃል፡፡
ስለሆነም የምዘና ቀን በ01/04/2013 ዓ.ም ስለሆነ የምዘናውን ቀን አውቃችሁ ከምዘና ማዕከል የሚመጡት አስተባባሪዎች የምዘና ኦረንቴሽን ስለሚሰጡ በ30/03/2013 ዓ.ም ከቀኑ በ10፡00 ስዓት ተገኝታችሁ የምዘና ኦረንቴሽን እንድትሳተፉ እያሳወቅን ይህ ሳይሆን ቢቀር ግን ለሚፈጠረው ችግር ኮሌጁ ተጠያቂ የማይሆን መሆኑን ከወዲሁ እንገልፃለን፡፡
ማሳሰቢያ፡-ለምዘና ስትቀርቡ 1 ፎቶ ግራፍ፣የምዘና አይዲ እና ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ ይዛችሁ መቅረብ አለባችሁ፡፡



ሬጅስትራር

19/11/2020
04/11/2020

ቁጥር ደ/ወ/ቴ/ኮ/2900/ትስ-13
ቀን 24/02/2013 ዓ/ም
ማስታወቂያ
በመጀመሪያ ዙር ለምትገቡ ነባር ሰልጣኞች በሙሉ
ከላይ በርዕሱ ለመግለፅ እንደተሞከረው በ2012 ዓ.ም በደብረ ወርቅ ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ በኮቪድ ወረርሽኝ ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን ስልጠና ለማስቀጠል ሰልጣኞችን በ3 ዙር ከፋፍሎ ማሰልጠን እንዳለበት በተሰጠን አቅጣጫ መሰረት በ2012 ዓ/ም ተመራቂ የነበራችሁና የተወሰነ የብቃት አሀድ የቀራችሁ የኮሌጁ ነባር ሰልጣኞች በመጀመሪያው ዙር ስልጠናችሁን ለመጀመር የመመዝገቢያ 100(አንድ መቶ ብር) በኮሌጁ አብቁተ ደ/ወርቅ ቅርንጫፍ የሂሳብ ቁጥር 160005100 ከ24/02/2013 ዓ/ም እስከ 28/02/2013 ድረስ የመመዝገቢያ ክፍያችንን ሙሉ በሙሉ በማካተት ከ30/02/2013 ዓ/ም ጀምሮ ስልጠናችሁን እንድትጀምሩ በጥብቅ እናሳውቃለን፡፡
የደ/ወርቅ/ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ በመጀመሪያው ዙር የሚገቡ ሰልጣኞች
ተ.ቁ የሙያ አይነት የገቡበት ደረጃ አሁን ያሉበት ደረጃ የሚገቡበት የስልጠና ዙር ስልጠና የጀመሩበት ዓ.ም ምርመራ
1 Surveying IV IV 1st 2010 25
2 Animal production and marketing management IV IV 1st 2010 39
3 Crop production and marketing management IV IV 1st 2010 42
4 Furniture making IV III 1st 2010 07
5 Apparel fashion design and supervision IV III 1st 2010 04
6 Database administration IV I 1st 2012 የማታ ሰልጣኞች

ማሳሰቢያ፡-
 ማንኛውም ሰልጣኝ የፊት ማስክ መልበስ የሙያውን አልባሳት ጋውን ወይም ቱታ መልበስ አለባችሁ፡፡
 የኮሌጁን መታወቂያ ይዞ መገኘት አስፈላጊ መሆኑን እየገለፅን ይህንን የማያደርግ ሰልጣኝ የማናስተናግድ መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን፡፡
 Database administration ለማታ ሠልጣኞች ሲሆን የቀኖች አይጨምርም
 Database administration የአንድ ወር ክፍያ ብር 300(ሦስት መቶ ብር ብቻ) በመክፍል ከላይ በተጠቀሰው ቀን ለስልጠና እንድትገኙ፡፡
 ለቀሩት ሙያዎች ወደፊት በማስታወቅያ የምናሳውቅ ይሆናል፡፡
“ከሠላምታ ጋር”

27/10/2020
24/06/2020

በደብረ ወርቅ ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ በጀማሪ ኢንስትራክተር አበጀ አዳሙ ኮቪድ-19 ለመከላከል ከእጅ ንክኪ ነፃ የሆነ የእጅ መታጠቢያ ተሰራ

20/06/2020

የፊታችን እሑድ በቀኑ ፀሐይ ትጨልማለች! ብርሃንዎን
እንዳያጡም ይጠንቀቁ

የፀሐይ ግርዶሽ የፈጣሪ ቁጣ ሳይሆን የተፈጥሮ ክስተት መሆኑን
በመገንዘብ
ክስተቱን መመዝገብ እንደሚገባ ሊቃውንት መክረዋል፡፡
የፊታችን እሑድ ሰኔ 14/2012 ዓ.ም በዓለም ሰማይ ላይ ፀሐይ
በጨረቃ
ትሸፈናለች፤ በከዋክብትም ትከበባለች፤ ሰማይም ልዩ ገጽታ
ይኖራታል፡፡
ያልሰሙት ሲደናገጡ የሰሙት ደግሞ ይደነቃሉ፡፡ ቀኑም የተለዬ
ይሆናል፡፡ ሰኔ
14 ቀን 2012 ዓ.ም ስለሚኖረው የፀሐይ ግርዶሽ ከአብመድ ጋር
ቆይታ
የነበራቸው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን
የሐዲሳት
መምህርና የጥንታዊ ጽሑፍ ታሪክ ተመራማሪ መጋቢ ሐዲስ ሮዳስ
ታደሰ
(ዶክተር) እና የአስትሮ ፊዚክስ ምሁሩ ዶክተር ጌትነት ፈለቀ ቀኑን
አስመልክተው የቀደሙት ኢትዮጵያውያን ዕወቅት እና የዘመኑን
ሳይንስ
እያጣቀሱ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
የጠፈር ምርምር ሰማያዊ አካላትን የሚመረምር ሳይንስ ነው፡፡
ኢትዮጵያውያንም በዚህ ዘርፍ ቀዳሚ ከነበሩ ሀገራት መካከል
የሚጠቀሱ
ናቸው፡፡ ጥንታዊ የጠፈር ምርምር ኢትዮጵያን ከአፍሪካ ሀገራት
ብቸኛዋ
ያደርጋታል፡፡ የሥነ ፈለክን ወይም የሥነ ከዋክብትን ጥናት የጀመሩ
ኢትዮጵያውያን እንደሆኑ ምሁራን ይናገራሉ፡፡ ስለፕላኔቶችም ስያሜ
የሰጡ
ሕዝቦች ናቸው፡፡ ከዛሬ አራት ሺህ ዓመት በፊት ከንግሥት
ካስዮፕያ እስከ
ባለቤቷ ሴፈስ፣ ከልጃቸው ልዕልት አንድሮሜዳ እስከኋለኞቹ
ኢትዮጵያውያን
ሊቃውንት በሰማይ ስላሉ አካላት በብራናቸው በማይጠፋ
ቀለማቸው ከትበው
አልፈዋል፤ በስማቸውም ሰይመዋቸዋል፡፡
ቆይቶ የተነሳው ግሪካዊው አስትሮኖመር ፕቶሎሚም 48 ኅብረ
ከዋከብትን
ሲመዘግብ ሦስቱን ለኢትዮጵያ ሰጥቶ ነበር፡፡ ዓለም አቀፉ
የአስትሮኖሚ
ኅብረት በ1930ዎቹ ሲመዘግብ በመጀመሪያ የመዘገበው የልዕልት
አንድሮሜዳዋን ስያሜ ኮከብ ነበር፡፡ ጠቢቡ ንጉሥ ላልይበላ
ከአንድ አለት ላይ
11 አብያተ ክርስቲያናትን ስለሠራ በዚህ ብቻ ስሙ ከፍ ቢልም
የሒሳብና
የሥነ ፈለክ ቀመርም ፈጥሯል፡፡ ንጉሡ ከማንም በመቅድም የራሱ
የሆነ
የሰማይ ምልከታ ቦታ እና መመልከቻ መሳሪያም ነበረው፡፡
በሕዋ ሳይንስ ከሚታወቀው የማይታወቀው እንደሚበልጥ ዶክተር
ጌትነት
ተናግረዋል፡፡ ቀደምት ኢትዮጵያውያን ስለግርዶሽ በሚገባ ጽፈው
እንዳስቀመጡ ደግሞ መጋቢ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
ተናግረዋል፡፡
በኢትዮጵያ ታሪክ አስደናቂና አስፈሪ የነበሩ ግርዶሾች
ስለመመዝገባቸው
ታሪኩን እያጣቀሱ ሊቃውንቱ አስረድተዋል፡፡ በ1545 ዓ.ም
ከአጽናፍ ሰገድ
አጼ ገላውዴዎስ እስከ አዕላፍ ሰገድ ጻዲቁ ዮሐንስ ኅዳር 5 ቀን
1661 ዓ.ም፣
ከጻዲቁ ንጉስ ዮሐንስ መጋቢት 24 ቀን 1672 ዓ.ም እስከ
ዳግመዊ
እስክንድር አጼ በካፋ 1720 ዓ.ም የፀሐይ ግርዶሽ ተከስቶ
እንደነበር ታሪክ
ይነግረናል፡፡ በተለይም በአፄ ባካፋ ዘመነ መንግሥት የነበረውን
ግርዶሽ መጋቢ
ሀዲስ ዶክተር ሮዳስ ታሪከ ነገሥትን ዋቢ አድርገው ሲያስረዱ
“ዳግማዊ
እስክንድር አጼ በካፋ በነገሠ በ6ኛው ዓመት በወርኃ መስከርም
በሰባተኛው
ቀን ሦስት ሰዓት ላይ ፀሐይ ጨለመች፡፡ ከዋክብትም ታዩ፣ ሰው
ሁሉ ታወከ፣
ለመኑም፣ ፀሐይም እንደገና በራች” በማለት ግርዶሹ ሲከሰት ሰው
እንዴት
ተደናግጦ እንደነበር አስረድተዋል፡፡ ቀደምት ኢትዮጵያውያን
ግርዶሽ ብቻ
ሳይሆን ጅራታማ ኮኮብ ሲታይም ከትበው አስቀምጠው ነበር፤
የዘንድሮው
ግርዶሽ ለዬት ያለ ግርዶሽ ስለመሆኑም ሊቃውንቱ አብራርተዋል፡፡
የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝንና የግርዶሹን መገጣጠም በተመለከተ
ደግሞ
‘‘ፀሐይ ሦስት ክፍሎች አሏት፤ የሚታዬው ብርሃናማው ክፍል
‘ፎቶስፌር’
ይባላል፣ ከሱ ቀጥሎ ያለው ውጫዊ ከባቢ አየር

13/06/2020

Well come Debre work tvet page

Address

Debre Work
Debre Werk'

Telephone

+251586630194

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Debre work TVET college posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share