Asrat Atsedeweyn

Asrat Atsedeweyn 5th President of the University of Gondar. Committed to institutional excellence, global partnerships, and the advancement of higher education in Ethiopia.

Bridging tradition with innovation for a brighter future.

"የጎንደር ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በጤና መረጃ ሥርዓትና በዲጂታል ለውጥ ያሳየው የላቀ ውጤት ተገምግሞ “የመረጃ አብዮት አርአያ ተቋም” ተብሎ መሸለሙ ለዩኒቨርሲቲው ብቻ ሳ...
26/06/2026

"የጎንደር ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በጤና መረጃ ሥርዓትና በዲጂታል ለውጥ ያሳየው የላቀ ውጤት ተገምግሞ “የመረጃ አብዮት አርአያ ተቋም” ተብሎ መሸለሙ ለዩኒቨርሲቲው ብቻ ሳይሆን ለመላው የጤና ዘርፍ ኩራት ነው።" ~
ክብርት ዶር መቅደስ ዳባ፣ የኢፌዴሪ ጤና ሚንስትር ካስተላለፉት መልዕክት የተወሰደ።
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
ሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም

The outstanding performance of the University of Gondar Comprehensive Specialized Hospital in the health information system and digital transformation has been evaluated, and its award as a 'Model Institution for Information Revolution' is a pride not only for the university but for the entire health sector." ​— Excerpt from the message delivered by H.E. Dr Mekdes Daba, Minister of Health, Minister of the Ministry of Health,Ethiopia
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
June 25, 2026
​ Lijalem Gashaw Binyam C. Tilahun Solomon Abrha Aynishet Adane Medical Information Afework Kassu Ministry of Education Ethiopia Ethiopian Medical Association

ኢትዮጵያን የሰው ዘር መገኛ (Land of Origins) ያስባለውን የታሪክ አሻራ ላኖሩት ለፕሮፌሰር ዶናልድ ካርል ጆሃንሰን የክብር ዶክትሬት ማበርከታችን ታላቅ ኩራት ነው! ​የጎንደር ዩኒቨ...
25/06/2026

ኢትዮጵያን የሰው ዘር መገኛ (Land of Origins) ያስባለውን የታሪክ አሻራ ላኖሩት ለፕሮፌሰር ዶናልድ ካርል ጆሃንሰን የክብር ዶክትሬት ማበርከታችን ታላቅ ኩራት ነው!

​የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሴኔት ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ፣ የሰው ልጅ አመጣጥ ሳይንስን መልክ ለቀየሩትና የ"ድንቅነሽ" (Lucy) አግኚ ለሆኑት ለታዋቂው ምሁር ፕሮፌሰር ዶናልድ ካርል ጆሃንሰን የክብር የሳይንስ ዶክትሬት (Doctor of Science, Honoris Causa) ዲግሪ ለመስጠት በሙሉ ድምፅ ወስኗል።

​ፕሮፌሰር ጆሃንሰን በ1974 እኤአ. በአፋር ምድር ያገኟት የ3.2 ሚሊዮን ዓመቷ ድንቅነሽ፣ የሰው ልጅ በሁለት እግሩ ቀጥ ብሎ መራመድ የጀመረው አእምሮው ከመገንባቱ በፊት መሆኑን በማረጋገጥ የዓለምን የሳይንስ ታሪክ የቀየረ ታላቅ ግኝት ነው። ይህ ግኝት ሳይንሳዊ እውነታን ብቻ ሳይሆን ሀገራችን ኢትዮጵያ የሰው ዘር በሙሉ መገኛና የጋራ ቤታችን መሆኗን በዓለም አቀፍ መድረክ በደማቁ እንድታውጅ አድርጎታል።

​የዘንድሮውን የ2018 ዓ.ም. የተማሪዎቻችንን ዓመታዊ ምረቃ በምናከብርበት በዚህ ታሪካዊ ሳምንት፣ ፕሮፌሰር ጆሃንሰን በዓለም አቀፍ ምርምር፣ በትምህርትና የኢትዮጵያን የቅሪተ-አካል ቅርሶች በመጠበቅና በማስተዋወቅ ላበረከቱት የዕድሜ ልክ ውለታ ይህንን ከፍተኛ ተቋማዊ እውቅና ስናበረክትላቸው በራሴና በዩኒቨርሲቲያችን ማኅበረሰብ ስም ታላቅ ክብርና ደስታ ይሰማናል።

​ይህ የክብር ዲግሪ የፕሮፌሰሩን የላቀ ሳይንሳዊ አበርክቶ የምናስብበት ብቻ ሳይሆን፣ የዛሬዎቹ ተመራቂዎቻችንና ወጣት ተመራማሪዎቻችን አድማስ ተሻጋሪ ለሆኑ የሳይንስ ግኝቶች እንዲተጉ የሚያነሳሳ ትልቅ የዕውቀት ፋና ነው።

ታዋቂው ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ዶናልድ ጆሃንሰን በምረቃው መርሐ-ግብር ላይ በዙም (Zoom) ቀጥታ መስመር በመግባት ለዕጩ ተመራቂዎች፣ ለቤተሰቦቻቸውና ለበዓሉ ታዳሚዎች በሙሉ ልዩ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት የሚያስተላልፉ በመሆኑ፣ ፕሮግራሙን በሁሉም ይፋዊ የማኅበራዊ ስርጭት መንገዶቻችን (Live Streams) እንድትከታተሉን በአክብሮት እንጋብዛለን!

ፕሮፌሰር ዶናልድ ጆሃንሰን ​እንኳን ወደ አንጋፋው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የክብር ቤተሰብነት በደህና መጡ!
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
ሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም.

​An absolute honor to welcome the legendary discoverer of "Lucy" into the University of Gondar family!

​I am immensely proud to announce that the Senate of the University of Gondar has officially voted to confer an Honorary Doctor of Science (Doctor of Science, Honoris Causa) degree upon the world-renowned paleoanthropologist, Professor Donald Carl Johanson.

​In 1974, Professor Johanson's historic discovery of the 3.2-million-year-old hominin fossil "Lucy" (Dinkinesh) in the Afar Region forever reshaped the global scientific understanding of human evolution. More importantly, his work provided the ultimate scientific evidence that crowned Ethiopia as the undisputed "Cradle of Humankind" and the "Land of Origins" for all of humanity.

​As we celebrate our 2026 Annual Graduation Week, conferring this highest institutional honor upon Professor Johanson is a testament to our deep appreciation for his lifelong dedication to global scholarship, education, and his unwavering commitment to preserving and promoting Ethiopia’s rich paleoanthropological heritage.

​By bringing this global icon into our academic fold, we aim not only to honor his enduring legacy but also to inspire our graduates and young researchers to pursue groundbreaking scientific inquiries that cross borders and impact humanity.

We are thrilled to share that Professor Donald Johanson will be joining our graduation ceremony live via Zoom to deliver a special address to our graduates, their families, and the entire university community. Tune in and follow the live broadcast across all our official media and streaming platforms!

​Welcome to the University of Gondar, Professor Donald Carl Johanson! Your scientific journey remains an in​spiration to us all.
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
June 25, 2026

Arizona State University U.S. Embassy Addis Ababa Ministry of Education Ethiopia Arizona State Sun Devils Arizona State University (ASU) Off Campus Housing & Roommate Search

ሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም. ለምትመረቁ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ!​በነገው ዕለት የሚካሄደው የዓመታዊ ምረቃ በዓል መድረክ ዝግጅት በከፊል ይህንን ይመስላል።፥፥፥፥፥...
24/06/2026

ሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም. ለምትመረቁ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ!

​በነገው ዕለት የሚካሄደው የዓመታዊ ምረቃ በዓል መድረክ ዝግጅት በከፊል ይህንን ይመስላል።
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
ሰኔ 16 ቀን 2018ዓ.ም.

Congratulations to the University of Gondar students graduating on June 25, 2026!

​This is partly what the stage preparation looks like for tomorrow's annual graduation ceremony.
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
June 23, 2026

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ የሚከተሉትን ስምንት እውቅ ምሁራን ከተባባሪ ፕሮፌሰርነት ወደ ሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ እድገት አጽድቋል፦፨​ ዶ/ር በውቀቱ መሐሪ፣፨​ ዶ/ር ሞላ ተፈራ...
24/06/2026

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ የሚከተሉትን ስምንት እውቅ ምሁራን ከተባባሪ ፕሮፌሰርነት ወደ ሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ እድገት አጽድቋል፦

፨​ ዶ/ር በውቀቱ መሐሪ፣

፨​ ዶ/ር ሞላ ተፈራ፣

፨​ ዶ/ር ምሳዬ ሙላቴ፣

፨​ ዶ/ር ጌትነት ማስረሻ፣

፨​ ዶ/ር ደሴ ጥበበ፣

፨​ ዶ/ር ማስተዋል ብርሀን፣

፨​ ዶ/ር አስማማው አጥናፉ እና

፨​ ዶ/ር አስማማው ዓለሙ።

​ይህ ከፍተኛ የአካዳሚክ ማዕረግ በአዲሱ የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር መመሪያ መሠረት በምርምር፣ በማስተማርና በላቀ ተቋማዊ አመራር ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የተሰጠ እድገት ነው።

​በዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት ስም ለእነዚህ አንጋፋ ምሁራን፣ ለቤተሰቦቻቸው እንዲሁም ለመላው የዩኒቨርሲቲያችን ማሕበረሰብ አባላት ለዚህ ታላቅ ስኬት እንኳን ደስ አላችሁ፤ እንኳን ደስ አለን ለማለት እወዳለሁ!
​፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
ሰኔ 17 ቀን 2018 ዓ.ም

​The University of Gondar Governing Board has officially approved the promotion of the following eight distinguished faculty members from the rank of Associate Professor to Full Professor:

፨​ Dr. Bewketu Mehari,

፨​ Dr. Molla Tefera,

፨​ Dr. Missaye Mulatie,

፨​ Dr. Getinet Masresha,

፨​ Dr. Dessie Tibebe,

፨​ Dr. Mastewal Birhan,

፨​ Dr. Asmamaw Atinafu, and

፨​ Dr. Asmamaw Alemu.

​This highest academic rank is awarded in accordance with the new FDRE Ministry of Education Ethiopia guidelines for their outstanding contributions to research, teaching, and institutional leadership.

​On behalf of the University management, I extend my heartfelt congratulations to the newly appointed Professors, their families, and the entire university community on this monumental achievement.
​፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
June 24, 2026

​ Lijalem Gashaw Aynishet Adane Medical Information Ministry of Education Ethiopia Binyam C. Tilahun Afework Kassu Ethiopian Medical Association Solomon Abrha

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ይጣራል።ኑ አብረን ታሪክ እንስራ! አብረን ታሪክ እንሰብስብ!አብረን ታሪክ እናስተላልፍ።ይህ ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ የቀረበ ጥሪ ነው። ታሪክ የሀገር ማንነት፣ የትውልድ መገናኛ...
22/06/2026

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ይጣራል።
ኑ አብረን ታሪክ እንስራ!
አብረን ታሪክ እንሰብስብ!
አብረን ታሪክ እናስተላልፍ።

ይህ ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ የቀረበ ጥሪ ነው። ታሪክ የሀገር ማንነት፣ የትውልድ መገናኛ ድልድይ ነው። ኢትዮጵያችን የረጅም ዘመን ታሪክ ባለቤት ብትሆንም፣ ብዙዎቹ የታሪክ ምስክር የሆኑ ቅርሶች፣ ሰነዶችና ቁሳቁሶች በተለያዩ ግለሰቦች እጅና በየቤቱ ተበታትነው ይገኛሉ። እነዚህ ቅርሶች በግለሰብ እጅ ሲቀሩ ከትውልድ እይታ ከመራቃቸውም በላይ፣ በአግባቡ ባለመያዛቸው ምክንያት የመጥፋት ወይም የመበላሸት አደጋ ተጋርጦባቸዋል። አንዳንዶች ደግሞ ቅርሶቹን የት እንደሚያስቀምጡ ወይም በምን መልኩ ለትውልድ ማስተላለፍ እንደሚችሉ ግራ ሊገባቸው ይችላል።

እንደ ዓለም ዩኒቨርሲቲዎች ሁሉ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ይህንን የታሪክ ክፍተት ለመሙላት፣ ቅርሶችን ለመሰነድ፣ ለጥበቃና ለምርምር አበርክቶ እንዲኖራቸው ለማድረግ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ አርካይቭ፣ ቤተ መዛግብት እና የዩኒቨርሲቲ ሙዚየም ማዕከላትን በአዲስ መልክ አደራጅቶ ሥራ ጀምሯል።

​በመሆኑም፤ ​በጥንታዊ የብራና ጽሁፎች፣ ደብዳቤዎችና ሰነዶች፣
​የታዋቂ አርበኞችና መሪዎች የግል መገልገያ ቁሳቁሶች (አልባሳት፣ የቤት ቁሳቁሶች፣ የጦር መሳሪያዎች...)፣ ​ጥንታዊ ፎቶግራፎችና ሌሎች የታሪክ አሻራዎች በእጃችሁ የሚገኝ ግለሰቦችና ቤተሰቦች፤ እነዚህን ቅርሶች ለትውልድ ይሻገሩ፣ ይጠኑ እና ለምርምር ዓላማ ይውሉ ዘንድ ጭምር ለዩኒቨርሲቲያችን አርካይቭና ሙዚየም ማዕከላት በስጦታ በማበርከት፣ ቅርሶቹ በዘመናዊ መንገድ ተጠብቀው ለታሪክ ተመራማሪዎችና ለሚቀጥለው ትውልድ እንዲተላለፉ እንድታደርጉ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

በዚህ ተግባርዎ በታሪክ መዝገብ ላይ ስምዎ በበጎነት ይነሳል፤ ቅርሱም የሀገር ሀብት ሆኖ ለዘላለም ይኖራል፤

​"ዛሬ የምናስቀምጠው ቅርስ፣ የነገው ትውልድ መማሪያ ነው!
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
ሰኔ 15 ቀን 2018ዓ.ም

The University of Gondar Calls Upon You!
​Come, let us make history together!
Let us collect history together!
Let us pass history down together!

​This is an official invitation from the University of Gondar. History is a nation's identity and a bridge that connects generations. Although our Ethiopia is endowed with a long and rich history, many historical artifacts, documents, and materials that bear witness to this heritage remain scattered in private hands and households. When these artifacts remain with individuals, they are hidden from public view and face the risk of being lost, damaged, or degraded due to a lack of proper preservation. Furthermore, many may find themselves uncertain about where to store these treasures or how to pass them down securely to future generations.

​Following the established practices of world class institutions, the University of Gondar is stepping forward to bridge this historical gap. To ensure the documentation, preservation, and research accessibility of these items, the university has newly restructured and launched the University of Gondar Archives, Records, and Museum Center.

​Therefore, we extend our call to all individuals and families who possess:
​Ancient manuscripts, historical letters, and archival documents, ​Personal effects of renowned patriots and leaders (such as clothing, household items, or weaponry), ​Vintage photographs and other historical footprints.

​We invite you to donate these invaluable artifacts to our University Archives and Museum Center. By doing so, you ensure they are preserved using modern conservation standards, made accessible to researchers, and passed down to future generations.

​Through this noble contribution, your name will be honorably inscribed in the records of history, and your artifacts will live on forever as national treasures.

​"The heritage we preserve today is the classroom for tomorrow's generation!"
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
​June 22, 2026

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የ2018 ትምህርት ዘመን ተመራቂዎች፣ የዓመታት የልፋታችሁ ፍሬ የሚታይበትና በስኬት የምትመረቁበት ዕለት አንድ ሳምንት ቀረው። ሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም. በደመቀ ሁኔታ...
18/06/2026

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የ2018 ትምህርት ዘመን ተመራቂዎች፣ የዓመታት የልፋታችሁ ፍሬ የሚታይበትና በስኬት የምትመረቁበት ዕለት አንድ ሳምንት ቀረው።

ሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም. በደመቀ ሁኔታ ለሚካሄደው የምረቃ ሥነ-ሥርዓት እንኳን በሰላም አደረሳችሁ!
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
ሰኔ 11 ቀን 2018ዓ.ም.

To the Class of 2026 graduates of the University of Gondar, you're just one week away from the day your years of hard work bear fruit and you graduate with success!

​Congratulations on reaching this grand graduation ceremony, which will be colorfully celebrated on June 25, 2026!
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
June 18, 2026

ከመቃብር በላይ የሚውል ስም ያለው፤ ሰማኸኝ!በባህላዊ ዜማዎቹ በተለይም ስለ አርሶ አደሩ ቱባ ሕይወት፣ ትጋት እና ክብር ልዩ ዜማዎችን የሰጠን፣ በባህላዊ አለባበሱና በልዩ የጥበብ ማንነቱ በሕ...
16/06/2026

ከመቃብር በላይ የሚውል ስም ያለው፤ ሰማኸኝ!

በባህላዊ ዜማዎቹ በተለይም ስለ አርሶ አደሩ ቱባ ሕይወት፣ ትጋት እና ክብር ልዩ ዜማዎችን የሰጠን፣ በባህላዊ አለባበሱና በልዩ የጥበብ ማንነቱ በሕዝብ ዘንድ እጅግ የሚወደደው አንጋፋው ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን ስንሰማ በጥልቅ ሐዘን ነው።

​ሰማኸኝ የኢትዮጵያን አርሶ አደር ድካምና ኩራት በዜማዎቹ ሕያው ያደረገ እውነተኛ የጥበብ ሰው ነበር። በራሱ ልዩ ዘይቤ የባህል ሙዚቃን ያደሰና ለኢትዮጵያ ኪነ-ጥበብ ትልቅ አሻራ ጥሎ ያለፈ ባለውለታ ነው። የእሱ ሕልፈት ለሀገራችን የኪነ-ጥበብ ዘርፍ በተለይም ለባህላዊው ሙዚቃ ትልቅ ጉድለት ነው። ይሁን እንጂ አርቲስት ሰማኸኝ በጥበብ ሥራዎቹ አብሮን የሚኖር፥ ከመቃብር በላይ ሊጠራ የሚችል ስም ያለው አርቲስት በመሆኑ በሥራዎቹ ሕያው ነው።

​በዚህ የሐዘን ወቅት ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ፣ ለሙያ አጋሮቹና ለአድናቂዎቹ በሙሉ ፈጣሪ መጽናናትንና ብርታትን እንዲሰጥ ከልብ እንመኛለን።

​የሰማኸኝ መልካም ሥራዎችና ስለ ገበሬው የዘመረላቸው የማይረሱ ዜማዎቹ በሕዝብ ልብ ውስጥ ምንጊዜም ሕያው ሆነው ይኖራሉ።

​ፈጣሪ ነፍሱን በገነት ያኑር!
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም

በትላንትናው ዕለት በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ኢንፎርማቲክስ ኮሌጅ አዘጋጅነት በተካሄደው የ"ቡና ወግ" (Coffee Talk) ዓመታዊ መርሐ-ግብር ላይ በእንግድነት ተገኝቼ ልምዴን ለታዳሚው የማካፈል...
16/06/2026

በትላንትናው ዕለት በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ኢንፎርማቲክስ ኮሌጅ አዘጋጅነት በተካሄደው የ"ቡና ወግ" (Coffee Talk) ዓመታዊ መርሐ-ግብር ላይ በእንግድነት ተገኝቼ ልምዴን ለታዳሚው የማካፈል ዕድል በማግኘቴ እጅግ ደስ ብሎኛል።

ይህ ፕሮግራም በህይወት ጉዟቸው ስኬታማ ሰዎችን ተሞክሮ ለተማሪዎች እና ለወጣት ተመራማሪዎች የሚያጋራ፣ ጠቃሚ እና አነቃቂ መድረክ ነው።

እንዲህ ዓይነት "ከመሪው ጀርባ" (Behind the Leader) የሚደረጉ መደበኛ ያልሆኑ ውይይቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ በታዋቂ ዩኒቨርሲቲዎች የሚዘወተሩ እና ትልቅ ፋይዳ ያላቸው መሆናቸውን ጥቂት ምሳሌዎችን ጠቅሰን ማየት ይቻላል፡-
ሀ. የሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ (Harvard University) - "Fireside Chats"

በሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ የኮሌጅ ዲኖች፣ ፕሬዝዳንቶች ወይም ታዋቂ የቀድሞ ተማሪዎች (Alumni) ከተማሪዎች ጋር ዘና ባለ መንፈስ በየጊዜው በትንንሽ አዳራሾች ውስጥ ይገናኛሉ። እዚያም መሪዎቹ የሕይወት እና የሥራ ጉዟቸውን (Leadership Journey) ግልጽ በሆነ መንገድ ያካፍላሉ።

ለ. የስታንፎርድ ዩኒቨርሲቲ (Stanford University) - "View From The Top"

ይህ በስታንፎርድ ቢዝነስ ትምህርት ቤት የሚዘጋጅ በጣም ታዋቂ ፕሮግራም ነው። ተማሪዎች ራሳቸው መድረኩን እየመሩ የዩኒቨርሲቲውን መሪዎች ጨምሮ የዓለም ታዋቂ የሥራ አስፈጻሚዎችን (CEOs) እና መሪዎችን ስለ ስኬታቸው፣ ስለ ውድቀታቸው እና ስለ ግል ሕይወታቸው ፈታኝ ጥያቄዎችን እየጠየቁ ልምድ ይገበያዩበታል።

ሐ. የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ (University of Oxford) - "Leadership in Extraordinary Times"
መሪዎች ከአካዳሚክ ማኅበረሰቡ ጋር በቅርበት በመቀመጥ፣ ወቅታዊ ዓለም አቀፍ ተግዳሮቶችን እንዴት እንደተወጡ እና ውሳኔ አሰጣጥ ላይ ምን ዓይነት ግልጽ መርሆችን እንደሚከተሉ የሚያወያዩበት መደበኛ ያልሆነ የውይይት መድረክ ነው።

እንደ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ፣ በአገራችን ወግና ባሕል መሠረት ለመርሐ-ግብሩ 'የቡና ወግ' (Coffee Talk) የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲሆን፣ የዚህ ዓይነቶቹ ፕሮግራሞች ፋይዳዎች እጅግ የጎሉ ናቸው፦

1. ለተማሪዎች እና ለወጣት ተመራማሪዎች፡

ሀ. እውነተኛ ተሞክሮን መቅሰም (Experiential Learning):
ተማሪዎች መሪዎችን በሩቅ ከመመልከት ይልቅ፣ የዛሬው የስኬት ደረጃ ላይ ለመድረስ ያለፉበትን ፈተና፣ የዕለት ተዕለት ውሳኔ አሰጣጥ እና የአመራር ጥበብ በቀጥታ ከአንደበታቸው ይማራሉ።

ለ. ተደራሽነት እና መነሳሳት (Inspiration): አንድን የከፍተኛ ትምህርት ኃላፊ (ለምሳሌ የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንትን) በቅርብ ርቀት ማግኘት መሪነት ሊደረስበት የሚችል የሕይወት ግብ መሆኑን ያሳያል፤ ተማሪዎች በትምህርታቸው እንዲበረቱ ትልቅ የውስጥ መነሳሳት (Motivation) ይፈጥርላቸዋል።

ሐ. የማኅበራዊ ትስስር (Networking): ከተራ የንግግር መድረክ ባለፈ፣ ተማሪዎች ከመሪዎች ጋር በቀጥታ ጥያቄና መልስ እንዲያደርጉና ሐሳብ እንዲለዋወጡ በር ይከፍታል።

2. ለዩኒቨርሲቲው እና ለመሪዎቹ፦
ሀ. ግልጽነት እና እምነት መገንባት (Transparency):
በአመራሩ እና በተማሪው/በሠራተኛው መካከል ያለውን የአስተዳደር ርቀት (Gap) ያጠባል። መሪው የራሱን ሰብዓዊ ጎን፣ ተግዳሮቶች እና ራዕዮች ለታዳሚው ሲያጋራ በተቋሙ ውስጥ መተማመን ይሰፍናል።

ለ. የሐሳብ መለዋወጫ መድረክ (Feedback Loop):
መሪዎች የተማሪዎቻቸውን እና የወጣት መምህራንን ወቅታዊ ስሜት፣ ፍላጎትና ስጋት ያለምንም መደበኛ ሪፖርት በቀጥታ የሚረዱበት ጥሩ አጋጣሚ ይሆናል።

እንዲህ ዓይነቱ የልምድ ልውውጥ መድረክ (የቡና ወግ) የመደበኛው የመማር-ማስተማር ሂደት አካል ባይሆንም፣ የተማሪዎችን፣ የወጣት መምህራንን እና የተቋሙን አመራሮች አስተሳሰብና ትስስር በማጠናከር ረገድ የማይተካ ሚና ይጫወታል። በመሆኑም፣ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የኢንፎርማቲክስ ኮሌጅ ይህንን መርሐ-ግብር ቀጣይነት ባለው መልኩ ለማስቀጠል ላሳየው ቁርጠኝነት፣ እንዲሁም መላው ተሳታፊ ላበረከተው የላቀ አስተዋጽኦ እና ንቁ ተሳትፎ ምስጋናዬን ለማቅረብ እወዳለሁ።

ወደፊትም ከሌሎች ኮሌጆች እና ክፍለ-ትምህርቶች ጋር በመተባበር፣ እንዲህ ያሉ አነቃቂ መድረኮችን በዩኒቨርሲቲያችን ለማስፋፋትና ተቋማዊ ባህል ለማድረግ የምናደርገውን ድጋፍ አጠናክረን እንቀጥላለን።
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
ሰኔ 9 ቀን 2018ዓ.ም

I'm immensely pleased to have had the opportunity to attend as a guest speaker and share my experiences at the annual "Coffee Talk" (የቡና ወግ) program yesterday, organized by the College of Informatics at the University of Gondar.
​This program serves as a valuable and inspiring platform that shares the experiences of successful individuals with students and young researchers.

​By looking at a few examples, we can see that such informal, "Behind the Leader" discussions are widely practiced at world-renowned universities and yield significant value:

​A. Harvard University – "Fireside Chats"

At Harvard University, college deans, presidents, or prominent alumni regularly meet with students in a relaxed atmosphere within small halls. There, leaders openly share their life and professional journeys (Leadership Journey).

​B. Stanford University – "View From The Top"

This is a highly popular program organized by the Stanford Graduate School of Business. Students themselves host the forum, engaging university leaders, global CEOs, and executives with challenging questions about their successes, failures, and personal lives to gain valuable insights.

​C. University of Oxford – "Leadership in Extraordinary Times"

This is an informal discussion forum where leaders sit closely with the academic community to discuss how they navigated current global challenges and the clear principles they follow in decision making.

​At the University of Gondar, in alignment with our country's tradition and culture, this program has been named "Coffee Talk" (የቡና ወግ), and the benefits of such initiatives are highly profound:

​1. For Students and Young Researchers:

​A. Experiential Learning:
Rather than observing leaders from a distance, students learn directly from their own words about the challenges they overcame to reach their current level of success, their daily decision-making processes, and the art of leadership.

​B. Accessibility and Inspiration:
Having close access to a higher education executive (such as a university president) demonstrates that leadership is an attainable life goal; it creates a powerful internal motivation for students to excel in their education.

​C. Networking:
Beyond a conventional speaking forum, it opens doors for students to engage in direct Q&A sessions and exchange ideas with leaders.

​2. For the University and its Leadership:

​A. Building Transparency and Trust:
It narrows the administrative gap between the leadership and the students or staff. When a leader shares their human side, challenges, and vision with the audience, it fosters institutional trust.

​B. Feedback Loop:
It provides an excellent opportunity for leaders to directly understand the current sentiments, needs, and concerns of their students and young faculty members without the filter of formal reports.

​Although this type of experience sharing platform (Coffee Talk) is not part of the formal teaching learning process, it plays an irreplaceable role in strengthening the mindset and connection among students, young faculty, and institutional leaders.

Therefore, I would like to express my gratitude to the University of Gondar's College of Informatics for its commitment to sustaining this program annually, as well as to all participants for their outstanding contributions and active engagement.

​Moving forward, we will continue to strengthen our support to expand such inspiring forums across our university and establish them as an institutional culture in collaboration with other colleges and departments.
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
​June 16, 2026

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ጥራትን፣ ፍትሃዊነትን እና አግባብነትን ለማሳደግ ያለመውን “Leaders in Teaching Ethiopia - LiTE) የተሰኘውን የለ...
14/06/2026

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ጥራትን፣ ፍትሃዊነትን እና አግባብነትን ለማሳደግ ያለመውን “Leaders in Teaching Ethiopia - LiTE) የተሰኘውን የለውጥ ፕሮግራም ለመተግበር ከኢማጂን ዋን ዴይ ጋር ታሪካዊ የመግባቢያ ስምምነት በይፋ መፈራረማችንን ለመግለጽ እወዳለሁ።

በሂደቱ ላሳዩን ደማቅ መስተንግዶ እና ፍሬያማ ውይይቶች ለኢማጂን ዋን ዴይ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ሰዒድ አማን እና ለመላ የሥራ ባልደረቦቻቸው ላቅ ያለ ምስጋናዬን ማቅረብ እወዳለሁ።

ኢማጂን ዋን ዴይ በኢትዮጵያ ጥራት ያለው ትምህርትን፣ የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትን እና የማህበረሰብ መሪነት ሞዴሎችን ለማስፋፋት በትጋት የሚሠራ ታዋቂ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ነው።

ቀጣዮቹን አምስት ዓመታት የሚሸፍነው ይህ ኢኒሼቲቭ ከትምህርት ሚኒስቴር እና ከማስተርካርድ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር በአገሪቱ በሚገኙ 700 ትምህርት ቤቶች ውስጥ ተግባራዊ ይደረጋል። ዩኒቨርሲቲያችን የዚህ ፕሮግራም ዋና አካዳሚያዊ እና አስተዳደራዊ ማዕከል ሆኖ ያገለግላል። በሥነ ትምህርት ኮሌጃችን በኩል የአስተማሪዎችን አቅም መገንባት፣ ከአዲሱ የብቃት-ተኮር ሥርዓተ-ትምህርት ጋር የተጣጣሙ ቀጣይነት ያለው የሙያ ማበልጸጊያ (CPD) ሞጁሎችን በጋራ ማዘጋጀት እና የአቻ ለአቻ የመማማሪያ መረቦችን መዘርጋት ላይ በትኩረት እንሰራለን።

በተለይም ይህ አጋርነት ለሥርዓተ ጾታ እኩልነት፣ ለአካቶ ትምህርት እና ለዲጂታል ሥነ ማስተማር (Digital Pedagogy) ትልቅ ትኩረት የሚሰጥ ሲሆን፣ ሴት መምህራንን ወደ አመራርነት ለማምጣት የሚያስችል ልዩ የሴት አመራሮች መድረክን ያካትታል።

ከኢማጂን ዋን ዴይ እና ከLiTE ጥምረት አጋሮች ጋር በመሆን ጠንካራ፣ አካታች እና ለወደፊቱ ዝግጁ የሆነ የትምህርት ሥርዓት በኢትዮጵያ ለመገንባት በጉጉት እንጠብቃለን።
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
ሰኔ 7 ቀን 2018ዓ.ም

I'm delighted to announce that the University of Gondar has officially signed a landmark Memorandum of Understanding with Imagine1day INGO to implement the transformative "Leaders in Teaching Ethiopia (LiTE) Program"!

I would like to extend my heartfelt thanks to Dr. Seid Aman, CEO of Imagine1Day, and his exceptional team for their wonderful hospitality and the highly productive discussions we shared during this process.

Imagine1Day is a dynamic non-governmental organization dedicated to developing high quality education, clean water access, and community leadership models across Ethiopia.

Spanning the next five years, this initiative, partnered with the Ministry of Education Ethiopia and the Mastercard Foundation, is set to elevate the quality, equity, and relevance of secondary education across 700 schools in Ethiopia.

As an institution deeply committed to national progress, our university will serve as a vital academic and administrative hub. Through our College of Education, we will spearhead teacher training, co-design Continuous Professional Development (CPD) modules aligned with the Competency Based Curriculum, and establish peer learning networks. Crucially, this partnership focuses heavily on gender equity and digital pedagogy, including a dedicated Female Leadership Pipeline to advance female educators into leadership roles.

Together with Imagine1day and the LiTE consortium partners, we look forward to fostering a resilient, inclusive, and future ready education system in Ethiopia.
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
June 14, 2026

#ኢትዮጵያ

በትላንትናው ዕለት እኔና ባልደረቦቼ ስድስት ኪሎ በሚገኘው «የፀሐይ እልፍኝ»  የፀሐይ አሳታሚ የምርምር ማዕከል ጉብኝት አድርገን፣ ፍሬያማ ውይይት አድርገናል።​የፀሐይ አሳታሚ መሥራችና ባለቤ...
12/06/2026

በትላንትናው ዕለት እኔና ባልደረቦቼ ስድስት ኪሎ በሚገኘው «የፀሐይ እልፍኝ» የፀሐይ አሳታሚ የምርምር ማዕከል ጉብኝት አድርገን፣ ፍሬያማ ውይይት አድርገናል።

​የፀሐይ አሳታሚ መሥራችና ባለቤት ለሆነው ወንድማችን ኤልያስ ወንድሙ እና ባለቤቱ ታዋቂዋ አርቲስት ብሩክታዊት ጌታሁን (ቤቲ ጂ) እና ባልደረቦቻቸው ላደረጉልን ሞቅ ያለ አቀባበል ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን አቀርባለሁ።

​ፀሐይ አሳታሚ የአገራችንን ታሪክ፣ ባህል እና ቅርስ ሰንዶ ለትውልድ የሚያስተላልፍ ዘመን ተሻጋሪ ተቋም ነው። በዓለም ዙሪያ ተበታትነው የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ምሁራንን እና ስለ ኢትዮጵያ ያጠኑ የውጭ አገር ተመራማሪዎችን በማፈላለግና በማሰባሰብ ረገድ የሚከተሉትን አንጸባራቂ ሥራዎች አከናውኗል፦
1. ​አያሌ ቁጥር ያላቸው አዳዲስ መጻሕፍትን በጥራት አሳትሟል።

2. ​ከገበያ የጠፉ ነባርና ንጥር ሥራዎችን (classics) እንደገና እያሳተመ አሰራጭቷል።

3. ​"International Journal of Ethiopian Studies" እንዲሁም "Ethiopian Journal of Religious Studies" የተሰኙ ዓለም አቀፍ ጥናታዊ መጽሔቶችን ያሳትማል።

4. ​በውጭ አገራት የመጻሕፍት አውደ-ርዕዮችንና ልዩ ልዩ ከጥበብና ከመጻሕፍት ጋር የተገናኙ ዝግጅቶችን ያቀርባል።

5. ​የአገር መሪዎችን (ከነገሥታቱ ጀምሮ እስከ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ድረስ) መጻሕፍት በጥራት አሳትሞ ለንባብ አብቅቷል።

6. ​በግል ደረጃም በርካታ ጠቃሚ ሥራዎችን አዘጋጅቶ አሳትሟል።

​በአሜሪካ አገር ከ28 ዓመታት በፊት የተቋቋመው ፀሐይ አሳታሚ፣ በአሁኑ ወቅት በአገራችን በአንድነት ፓርክ ውስጥ እና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስድስት ኪሎ ግቢ (ታሪካዊው የካቲት 12 መታሰቢያ ትይዩ በሚገኘው የፎረም ሕንጻ ሥር) የፀሐይ የምርምር ማዕከል ከፍቶ በመሥራት ላይ ይገኛል።

በቀጣይም ኢትዮጵያን የእፍሪካ የዕውቀት ማዕክል የሚያደርጉና አገራችንንም ብቃት የሚያግዙ ስራዎችን እየሰሩ ይገኛል።

​የአቶ ኤልያስ ባለቤትና ሁላችንም የምናከብራት አርቲስት ብሩክታዊት ጌታሁን (ቤቲ ጂ) በበኩሏ በረቂቅ የጥበብ ሥራዎቿ አገሯን በዓለም አደባባይ እያስጠራች ትገኛለች። እዚህ ላይ አንድ ወንድሜ የነገረኝን ገጠመኝ ማጋራት ይገባኛል። "Kinokuniya" የተባለ ዓለም አቀፍ የጃፓን የመጻሕፍት መደብር አለ፤ ይህ ወንድሜ በሲንጋፖር በሚገኘው ቅርንጫፍ ውስጥ መጻሕፍት እየመረጠ ሳለ የቤቲ ጂ ሙዚቃ በመደብር ውስጥ ይሰማና በደስታ ይፈነጥዛል። "በሰው አገር፣ ያውም በትልቅ የመጻሕፍት መደብር ውስጥ የአገሬን ሙዚቃ ስሰማ ሰውነቴን ነዘረኝ፤ ደስታዬን የሚያጋራኝ ሰው በአቅራቢያዬ በማጣቴ ግን ቆጨኝ" ብሎ በስልክ ነግሮኛል። የቤቲ ጂ ዓለም አቀፋዊ ተጽዕኖ በኖቤል የሽልማት ሥነ ሥርዓት ላይ እንድታቀነቅን መመረጧ ብቻ በቂ ምስክር ነው።

​ፀሐይ አሳታሚ ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ ከዩኒቨርሲቲያችን ጋር የአጋርነት ስምምነት ተፈራርሞ እየሠራ ይገኛል። በቅርቡ የጀመርነው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ (UoG Press) እውን መሆንና በቀጣይም ፕሬሱ የሚጠበቅበትን አገራዊና ሳይንሳዊ ተልዕኮ በስኬት እንዲወጣ የፀሐይ አሳታሚ አጋርነትና ተሞክሮ ወሳኝ ነው።

​አቶ ኤልያስ ወንድሙና ባለቤቱ አርቲስት ብሩክታዊት (ቤቲ ጂ) ላደረጉልን አቀባበልና ፍሬያማ ውይይት በራሴና በባልደረቦቼ ስም ከልብ አመሰግናለሁ!
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
ሰኔ 5 ቀን 2018ዓ.ም
Yesterday, my colleagues and I visited the "Tsehai Pavilion" (የፀሐይ እልፍኝ) Tsehai Publishers Research Center located in Six Kilo, where we held a highly productive discussion.

​I would like to extend my heartfelt gratitude to our brother Elias Wondimu, the founder and owner of Tsehai Publishers, his wife, the renowned artist Bruktawit Getahun (Betty G), and their colleagues for the exceptionally warm welcome they accorded us.

Tsehai Publishers is a timeless institution that documents and passes down our country's history, culture, and heritage to future generations. By searching for and bringing together Ethiopian scholars scattered across the globe, as well as foreign researchers who study Ethiopia, it has accomplished the following brilliant works:
1. ​It has published a vast number of new books with high quality.

2. ​It has been republishing and distributing out of print, classic works. ​

3. It publishes international academic journals, namely the "International Journal of Ethiopian Studies" and the "Ethiopian Journal of Religious Studies".

4. ​It hosts book fairs and various art and book related events abroad.

5. ​It has published high-quality books by national leaders, spanning from the emperors to Prime Minister Abiy Ahmed, making them accessible to readers.

6. ​It has also prepared and published numerous valuable works on an individual level.

​Established 28 years ago in the United States, Tsehai Publishers is currently operating Tsehai Research Centers in our country within Unity Park and inside the Addis Ababa University Six Kilo Campus (located on the ground floor of the Forum Building, directly opposite the historic Yekatit 12 Monument).

​Moving forward, they continue to engage in endeavors that will position Ethiopia as Africa's hub of knowledge and enhance our country's capabilities.

​For her part, Mr. Elias's wife, Artist Bruktawit Getahun (Betty G), whom we all deeply respect, continues to uplift her country's name on the global stage through her profound artistic works. Here, I must share an anecdote a brother of mine told me. There is an international Japanese bookstore chain called "Kinokuniya." While this brother of mine was browsing books at the Singapore branch, Betty G's music started playing inside the store, making him leap with joy. He told me over the phone: "When I heard my country's music in a foreign land, and in a massive bookstore at that, a thrill ran through my entire body; however, I regretted not having anyone nearby to share my joy with." Betty G's global impact is sufficiently evidenced by her selection to perform at the Nobel Peace Prize ceremony.
​Tsehai Publishers has been working in partnership with our university since signed an agreement in 2018 G.C. The partnership and experience of Tsehai Publishers are crucial for the realization of the recently launched University of Gondar Press (UoG Press), and for ensuring the Press successfully fulfills its expected national and scientific mission in the future.

​On behalf of myself and my colleagues, I offer my deepest thanks to Mr. Elias Wondimu and his wife, Artist Bruktawit (Betty G), for the hospitality and fruitful discussion they provided us!
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
​June 12, 2026

Address

Maraki
Gondar
P.O.BOX196

Opening Hours

Monday 08:00 - 17:00
Tuesday 08:00 - 17:00
Wednesday 08:00 - 17:00
Thursday 08:00 - 17:00
Friday 08:00 - 17:00

Telephone

+251581141231

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Asrat Atsedeweyn posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The University

Send a message to Asrat Atsedeweyn:

Share