Asrat Atsedeweyn

Asrat Atsedeweyn 4th President of Addis Ababa Science and Technology University. University for Industry!

Committed to academic excellence, innovative research, and global partnerships, advancing technological transformation and industry-driven development in Ethiopia.

አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ — ለኢንዱስትሪ የተመሠረተ ዩኒቨርሲቲ!​ቴክኖሎጂ የሚቀርፀውን፣ ፈጠራን የሚያነቃቃውን እና ኢንዱስትሪን የሚያሻሽለውን አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ...
15/08/2026

አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ — ለኢንዱስትሪ የተመሠረተ ዩኒቨርሲቲ!

​ቴክኖሎጂ የሚቀርፀውን፣ ፈጠራን የሚያነቃቃውን እና ኢንዱስትሪን የሚያሻሽለውን አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲን ሳስተዋውቃችሁ በታላቅ ደስታ ነው።

🔬 ዘመናዊ የምርምርና የላቦራቶሪ ማዕከላት፣
💡 የፈጠራ ሥራዎችና የሥራ ፈጠራ (Entrepreneurship)፣
🎓 በኢንዱስትሪ ላይ ያተኮረ ትምህርት፣
🌍 ዓለም አቀፍ አጋርነቶች፣
🏭 ለኢንዱስትሪ የተመሰረተ ዩኒቨርሲቲ፣

👉 እባክዎን Like, Follow እና Subscribe በማድረግ ለኢትዮጵያ ዕድገትና ትራንስፎርሜሽን የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ፈጠራ ጉዞ አብረውን ይቀላቀሉ!

📘 ፌስቡክ: https://www.facebook.com/share/199L1YBYb1/

💼 ሊንክድኢን: https://bit.ly/aastu_officialin

▶️ ዩቲዩብ: https://youtube.com/?si=Q39l7qGu-NetmR4D

📱 ቴሌግራም: t.me/pir2011

🌐 ድህረ ገጽ: aastu.edu.et

📧 ኢሜይል: [email protected] | [email protected]

አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ - ማስተማር ብቻ አይደለም፤ የነገውን ብሩኅ ተስፋ እንቀርጻለን!

ዩኒቨርሲቲ ለኢንዱስትሪ፤ ፈጠራ ለማኅበረሰብ!
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
ነሐሴ 9 ቀን 2018ዓ.ም

Discover Addis Ababa Science and Technology University — University for Industry!

I'm proud to introduce Addis Ababa Science and Technology University (AASTU) — a university shaping technology, inspiring innovation, and transforming industry.

🔬 Cutting-edge research & laboratories
💡 Innovation & entrepreneurship
🎓 Industry-focused education
🌍 Global partnerships
🏭 University for Industry

👉 Please Like, Follow & Subscribe and join us in advancing science, technology and innovation for Ethiopia’s transformation!

📘 Facebook: https://www.facebook.com/share/199L1YBYb1/

💼 LinkedIn: https://bit.ly/aastu_officialin

▶️ YouTube: https://youtube.com/?si=Q39l7qGu-NetmR4D

📱 Telegram: t.me/pir2011

🌐 Website: https://www.aastu.edu.et

📧 Email: [email protected] | [email protected]

Addis Ababa Science and Technology University — It’s not just about teaching; we shape tomorrow's bright future!

University for Industry; Innovation for Society!
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
August 15, 2026

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የሀገራችንን የሳይበርና የመረብ ደህንነት በጽናት ከማስጠበቅ ባሻገር፣ የወደፊት ተተኪዎችንና አዲሱን ትውልድ የመቅረጽና የማብቃት ሥራዎችን በተግባር እ...
11/08/2026

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የሀገራችንን የሳይበርና የመረብ ደህንነት በጽናት ከማስጠበቅ ባሻገር፣ የወደፊት ተተኪዎችንና አዲሱን ትውልድ የመቅረጽና የማብቃት ሥራዎችን በተግባር እያረጋገጠ በመሆኑ ከፍተኛ አክብሮትና ምስጋና ይገባዋል።

የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ከተጣለበት የሀገራችንን የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፎች ማሳደግና ማላቅ መደበኛ ሀገራዊ ተልዕኮ በተጨማሪ፣ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የወጣት ታለንቶችን ለማልማት የጀመረውን አርአያነት ያለው በጎ እንቅስቃሴ ስኬታማ ለማድረግ ባለፉት አራት ዓመታት ሲያደርግ የነበረውን ድጋፍ አጠናክሮ ይቀጥላል።

ከአኩሪ የረጅም ዘመናት ታሪካችን ጋር የሚመጥን ሁለንተናዊ ልማትና ብልጽግናን ለማረጋገጥ በሳይንስና ቴክኖሎጂ መታጠቅ ይኖርብናል። ጃፓን፣ «የእስያ ነብሮች» በመባል የሚታወቁት እነ ሲንጋፖር፣ ደቡብ ኮሪያና ታይዋን፣ እንዲሁም ቻይና በቁጭት መንፈስ በመነሳት ከነበሩበት አሳዛኝ ሁኔታ ወጥተው ተአምራዊ ዕድገት ማስመዝገብ ችለዋል። «መስፈንጠር» (Leapfrogging) የሚለው የልማት አስተሳሰብም ከእነሱ የታሪክ ጉዞ የተቀሰመ ነው።

እኛም እንችላለን!!!
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
ነሐሴ 5 ቀን 2018ዓ.ም

The INSA- የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር deserves great respect and gratitude, not only for steadfastly safeguarding our nation’s cyber and network security, but also for actively engaging in shaping and empowering the next generation.

In addition to its national mandate to advance and elevate the country’s science and technology sectors, Addis Ababa Science and Technology University will strengthen the support it has been providing for the past four years to ensure the success of the administration’s exemplary initiative to nurture young talent.

To achieve holistic development and prosperity that matches our long, proud history, we must equip ourselves with science and technology. Japan, the 'Asian Tigers', such as Singapore, South Korea, and Taiwan, and China rose with a spirit of determination, emerging from difficult circumstances to achieve miraculous growth. The concept of development through 'leapfrogging' draws directly from their historic journey.

We can do it too!
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
August 11, 2026

​ #እንችላለን

በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የተጣለብኝን አዲስ አገራዊ ኃላፊነት ከመላው የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ ጋር በመሆን፣ ከፍተኛ ትርጉም ባለውና ታላቅ አገራዊ ፋይዳ ባለው የችግኝ ተከ...
05/08/2026

በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የተጣለብኝን አዲስ አገራዊ ኃላፊነት ከመላው የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ ጋር በመሆን፣ ከፍተኛ ትርጉም ባለውና ታላቅ አገራዊ ፋይዳ ባለው የችግኝ ተከላ መርሐ-ግብር በይፋ ጀምሬአለሁ።

​ዛሬ የተከልነው ችግኝ ለሥራ የተመቸ ንጹሕና አረንጓዴ ከባቢን ለመፍጠር እና የተፈጥሮ ሚዛንን ለመጠበቅ ለሚደረገው አገራዊ ጥረት የሚያበረክተው አስተዋጽዖ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ከመላው የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ ጋር ያለንን ትስስርና መተዋወቅ የሚያጠናክር፣ እንዲሁም የተጣለብንን ከፍተኛ አገራዊ አደራ በጋራ ለመወጣት የገባነው ቃልኪዳን መነሻ በመሆኑ ልዩ ትርጉም የሚሰጠው ነው።

​ዛሬ የምንተክለው ችግኝ የነገዋን አረንጓዴ፣ ለምና ውብ ዩኒቨርሲቲ የምንገነባበት ጠንካራ መሠረት ነው። ንጹሕና ምቹ የሥራ ከባቢ ለመማር-ማስተማሩ ሂደት ብቻ ሳይሆን ለፈጠራም (Innovation) ከፍተኛ አስተዋጽዖ አለው።

የቀደሙት የሥራ መሪዎችና ነባር ሠራተኞች በጀመሯቸው መልካም ተግባራት ላይ እየገነባን፣ አገርና ወገን የሚኮሩበትን ተቋም ለመፍጠር የሚጠበቅብንን ሁሉ እናደርጋለን።

​በአገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውንና የሚታይ ውጤት እያስመዘገበ የሚገኘውን የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ በመደገፍ፣ የተሻለችና አረንጓዴ የሆነች ኢትዮጵያን ለነገው ትውልድ ለማስረከብ የሚደረገው ጥረት አካል በመሆን የበኩላችንን ድርሻ በብቃት እንወጣለን!
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
ሐምሌ 29 ቀን 2018ዓ.ም

I have officially assumed my new national responsibility at Addis Ababa Science and Technology University alongside our entire university community, inaugurating my tenure with a highly meaningful tree-planting program of great national significance.

​Beyond its contribution to national efforts aimed at creating a clean, green, and conducive work environment while preserving the ecological balance, the trees we planted today hold special meaning. They serve as a foundation for our pledge to collectively fulfill our high national trust, while strengthening our bond and mutual acquaintance with the entire university community.

​The saplings we plant today lay a solid foundation for building tomorrow’s green, prosperous, and beautiful university. A clean and comfortable working environment contributes significantly not only to the teaching-learning process but also to innovation.

Building upon the good work initiated by past leaders and longstanding staff, we will do everything expected of us to create an institution that our nation and citizens can be proud of.

​By supporting the Green Legacy Initiative, which has been launched nationwide and continues to yield tangible results, we will effectively fulfill our role as part of the broader effort to pass on a better and greener Ethiopia to the next generation!
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
​August 5, 2026

አዲስ የኃላፊነት ምዕራፍ፡ የክብር ሽኝትና የላቀ አገራዊ ተልዕኮ ጅምር!​በሕይወቴና በአመራር ዘመኔ እጅግ ታሪካዊና ትርጉም ያላቸውን ሁለት ቀናት አሳልፌያለሁ። አንዱን ታላቅ የሕዝብ አደራ በ...
29/07/2026

አዲስ የኃላፊነት ምዕራፍ፡ የክብር ሽኝትና የላቀ አገራዊ ተልዕኮ ጅምር!

​በሕይወቴና በአመራር ዘመኔ እጅግ ታሪካዊና ትርጉም ያላቸውን ሁለት ቀናት አሳልፌያለሁ። አንዱን ታላቅ የሕዝብ አደራ በክብር አጠናቅቄ፣ ሌላኛውን አገራዊ የልህቀት ተልዕኮ በአዲስ መንፈስ ተረክቢያለሁ።

​1. ውድ የጎንደር ሕዝብና የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማኅበረሰብ፦
እጅግ አመሰግናለሁ!

​በጎንደር ዩኒቨርሲቲ በስታትስቲክስ መምህርነት፣ በትምህርት ክፍል ሊቀመንበርነት፣ በኮሌጅ ዲንነት፣ በጥናትና ምርምር ዳይሬክተርነት፣ በአካዳሚክ ምክትል ፕሬዚዳንትነት እና በመጨረሻም ላለፉት 7 ዓመታት ተኩል በፕሬዚዳንትነት በድምሩ ላለፉት 18 ዓመታት ያገለገልኩበትን የሥራ ኃላፊነት በክብር አጠናቅቄ ለአዲሱ ተተኪዬ ዶ/ር የቻለ ከበደ በትላንትናው ዕለት (ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ.ም) አስረክቤያለሁ።

​በእነዚህ ዓመታት ውስጥ ከደጉ የጎንደር ሕዝብና ከዩኒቨርሲቲያችን ማኅበረሰብ ብዙ ተምሬያለሁ። በተለይም ተቋሙን እንደ ዓይኑ ብሌን የሚንከባከበውና የሚጠብቀው የጎንደር ሕዝብ በሁሉም ፈታኝና መልካም ወቅቶች ያደረገልኝ ድጋፍና እገዛ በቃላት የማይገለጽ ነው። እኔና ባልደረቦቼ የቀደሙት መሪዎች በገነቡት መሠረት ላይ ተጨማሪ ጡብ ለመደርደር የቻልነውን ሁሉ ጥረናል፤ ውጤቱንም የታሪክና የሕዝብ ምስክርነት ያሳየዋል።

​ለእኔ የነበረው አጋርነትና ድጋፍ ለአዲሱ ፕሬዚደንት ዶ/ር የቻለ ከበደም ተጠናክሮ እንዲቀጥል አደራ እያልኩ፣ አዲሱ አመራር "እንደ አንድ ልብ መካሪ፣ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ" በመሆን ይህን አንጋፋ ተቋም ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያራምደው ሙሉ ተስፋ አለኝ።

​2. ለአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፦
አዲስ ምዕራፍ፣ አዲስ ተስፋ!

​ዛሬ (ሐምሌ 22 ቀን 2018 ዓ.ም) ደግሞ መንግሥትና ሕዝብ የሰጡኝን አዲስ አገራዊ ኃላፊነት ለመወጣት በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ተገኝቼ ሥራ ጀምሬያለሁ። በዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት እና መማክርት አባላት ለተደረገልኝ ሞቅ ያለ አቀባበልና የትውውቅ መርሐ-ግብር ልባዊ ምስጋናዬን አቀርባለሁ።

​ላለፉት 7 ዓመታት ተቋሙን በታማኝነትና በላቀ አርአያነት ሲመሩ ከቆዩት ዶ/ር ደረጀ እንግዳ ጋር ይፋዊ የሥራ ርክክብ አድርገናል። ዶ/ር ደረጀና መላው የተቋሙ ማኅበረሰብ ያስመዘገቧቸው ስኬቶች ለቀጣዩ ጉዟችን እጅግ ጠንካራ መሠረቶች ናቸው። ላበረከቱት የላቀ አስተዋጽኦም ታላቅ ክብርና ምስጋና ይገባቸዋል።

​3. የወደፊት ራዕያችን
​መንግሥት ከፍተኛ ትኩረት የሰጠውን ይህንን የቴክኖሎጂና የምርምር ማዕከል የመምራት ዕድል ማግኘቴን እንደ ትልቅ አገራዊ ዕድልና ክብር እቆጥረዋለሁ። በቀጣይም፦

ሀ. ​ተቋሙ የጀመራቸውን አዎንታዊና ውጤታማ ሥራዎች ከአዳዲስ ስትራቴጂካዊ ዕቅዶች ጋር በማቀናጀት ወደ ላቀ የልህቀት ምዕራፍ እናሸጋግራለን።

ለ. ​የዩኒቨርሲቲውን መሪ ቃል "ዩኒቨርሲቲ ለኢንዱስትሪ" (University for Industry) በተግባር እውን ለማድረግና አገራዊ የኢኮኖሚ ትስስሩን ለማጠናከር ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እንሠራለን።

​በመጨረሻም፣ ይህንን አንጋፋ ተቋም እንድመራ አምነው ኃላፊነት የሰጡኝን የመንግሥት አካላት፣ በአዲሱ ጉዞዬ አብረውኝ ለመሥራት ቁርጠኝነታቸውን ላሳዩኝ ለአሳቴዩ ሠራተኞችና ማኅበረሰብ፣ እንዲሁም በሥራ መደራረብ ምክንያት በበቂ ሁኔታ ጊዜ ላልሰጠኋቸውና ሁሌም ከጎኔ ቆመው ለሚደግፉኝ ውድ ቤተሰቦቼ ምስጋናዬ የላቀ ነው።

​ፈጣሪ አዲሱን የሥራ ዘመናችንን የተሳካና ፍሬያማ ያድርግልን!

ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
ሐምሌ 22 ቀን 2018ዓ.ም

A New Chapter of Responsibility: A Dignified Farewell and the Start of a Greater National Mission!

​Over the past two days, I have experienced deeply historic and meaningful moments in my life and leadership journey. I have honorably completed one great public trust and taken up another national mission of excellence with a renewed spirit.

​1. To the Beloved People of Gondar and the University of Gondar Community: Thank You Deeply!

​Yesterday (July 28, 2026, I officially handed over my leadership responsibilities to my successor, Dr. Yechale Kebede Bizuneh. This marks the completion of my service at the University of Gondar spanning a total of 18 years, during which I served as a Statistics Lecturer, Department Head, College Dean, Director for Research and Publication, Academic Vice President, and ultimately, as President for the last 7.5 years.

​Throughout these years, I've learned so much from the kind people of Gondar and our university community. In particular, the support and encouragement I received through every challenging and triumphant time from the people of Gondar, who cherish and protect the institution like the apple of their eye, is beyond words.

Alongside my colleagues, we've done our utmost to build upon the foundation laid by previous leaders; history and the testimony of the public will bear witness to our achievements.

​While urging that the same solidarity and support be extended to the new President, Dr. Yechale, I am fully confident that the new leadership team will move "with one heart and one voice" to elevate this historic institution to even greater heights.

​2. To Addis Ababa Science and Technology University (AASTU): A New Chapter, A New Hope!

​Today (July 29, 2026), I commenced my duties at Addis Ababa Science and Technology University to fulfill the new national responsibility entrusted to me by the government and the public. I express my heartfelt gratitude to the university management and senate members for the warm welcome and introductory program.

​I have officially completed the leadership transition with Dr. Dereje Engida, who has served the institution with loyalty and distinction for the past 7 years. The milestones achieved by Dr. Dereje and the entire university community serve as a solid foundation for our journey ahead. Great honor and appreciation go to him for his outstanding contributions.

​3. Our Future Vision
​I consider the opportunity to lead this center of technology and research, which the government holds in high regard, a profound national privilege and honor. Going forward, we will:

​A. Advance the positive and impactful initiatives already started by the institution, integrating them with new strategic plans to transition into a higher chapter of excellence.

B. Work collaboratively with all stakeholders to realize the university's motto, "University for Industry," and strengthen national economic integration.

​Finally, my deepest gratitude goes to the government bodies that entrusted me with the responsibility to lead this prestigious institution, to the staff and community of AASTU for showing their commitment to working alongside me in this new chapter, and to my dear family, who have always stood by me and supported me despite the heavy workload that often limited my time with them.

​May the Almighty make our new tenure successful and fruitful!

​God Bless Ethiopia and its People!
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
​July 29, 2026

Ministry of Education Ethiopia Lijalem Gashaw Aynishet Adane

ታሪክ፣ ዘላቂ ትሩፋት እና ታላቅ ራዕይ ወደ አዲስ ምዕራፍ!​የእውነተኛ ፍቅር፣ የከበረ በጎ አድራጎት እና ለሀገርና ለወገን የመኖር ታላቅ አርአያ የሆኑት የክቡር ዶ/ር በርናርድ አንደርሰን (...
28/07/2026

ታሪክ፣ ዘላቂ ትሩፋት እና ታላቅ ራዕይ ወደ አዲስ ምዕራፍ!

​የእውነተኛ ፍቅር፣ የከበረ በጎ አድራጎት እና ለሀገርና ለወገን የመኖር ታላቅ አርአያ የሆኑት የክቡር ዶ/ር በርናርድ አንደርሰን (የጃማይካው ጎንደሬ) እና የሕይወት አጋራቸው የሲስተር እማዋይሽ ገሪማ ዘላቂ ራዕይ ወደ አዲስ ታሪካዊ ምዕራፍ ተሸጋግሯል።

​የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከሲስተር እማዋይሽ ገሪማ የኑዛዜ ወራሾች፣ ከተጠቃሚዎች እና ከባለአደራ እንደራሴያቸው ከአቶ ዳዊት ደርበው ጋር በመሆን፣ ግንባታው የተጀመረውን ሆስፒታል ሙሉ በሙሉ አጠናቆ ለሕዝብ አገልግሎት ለማዋል ታሪካዊ የጋራ መግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል።

​ይህ ውሳኔ የሁለቱን ታላላቅ ባለውለታዎች ስም ከመዘከር ባለፈ፣ ለሀገራችን የጤና እና የትምህርት ዘርፍ ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታዎችን ይዞ የመጣ ነው፡

​1. የዕንቁው የውርስ ስጦታ (Endowment) ዘላቂነትና ዋስትና፦
​ባለ 70 መኝታው ዘመናዊ ሆስፒታልና ሙዚየም ወደ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ መካተቱ፣ ፕሮጀክቱ በጠንካራ ተቋማዊና ሕጋዊ ማዕቀፍ እንዲመራ ያደርገዋል። ይህም የባለእምነቶቹ ውርስና ንብረት (Endowment) ሳይበረዝ፣ ሳይከለስና ሳይቋረጥ ለታለመለት የሕዝብ ጥቅም ለዘላለም እንዲውል ሙሉ ዋስትና ይሰጣል።

​2. ጎንደርን የሕክምና ቱሪዝም (Medical Tourism) መዳረሻ ማድረግ፦
​ዶ/ር በርናርድ በሕይወት እያሉ ያስጀመሯቸውን የጉበት፣ የጣፊያ፣ የልብና የደም ሥር የቀዶ ሕክምና ስፔሻሊቲዎችን ይበልጥ በማስፋፋት፣ ማዕከሉ ከፍተኛ ጥራት ያለው የሕክምና አገልግሎት የሚሰጥበት ይሆናል። ይህ ደግሞ ከሀገር ውስጥ አልፎ ከጎረቤት ሀገራት ጭምር ሕሙማንን በመሳብ ጎንደርን የሕክምና ቱሪዝም መዳረሻ ያደርጋታል፤ የሀገሪቱንም የውጭ ምንዛሬ ፍሰት ያግዛል።

​3. የምርምርና የልህቀት ማዕከል፦
​ይህ ተቋም የሕክምና አገልግሎት ብቻ ሳይሆን፣ ለቀጣይ ትውልድ ሐኪሞች ጥራቱን የጠበቀ የድኅረ-ምረቃ ስልጠናና የምርምር ማዕከል በመሆን ያገለግላል። ዶ/ር በርናርድ በዩኒቨርሲቲያችን የጣሉት የማይረሳ የአካዳሚክ አሻራ አሁን ይበልጥ እንዲያብብ መንገድ ይከፍታል።

​“የጃማይካው ጎንደሬ” ዶ/ር በርናርድ አንደርሰን ማን ነበሩ?

​ዶ/ር በርናርድ አንደርሰን እ.አ.አ. በ1937 ጃማይካ ውስጥ ተወልደው፣ በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ እጅግ የተደላደለና ታዋቂ የቀዶ ጥገና ሐኪም የነበሩ ቢሆንም፣ “ወደ ጥቁር ሕዝብ መኩሪያ፣ ወደ እውነተኛዋ የትሕትና ምድር እንመለስ” የሚለውን ጥሪ ተቀብለው በ1997 ዓ.ም. ሙሉ ሕይወታቸውን ለጎንደር ሕዝብ ሰጥተዋል።

​የፍቅርና የትሕትና ተምሳሌት፡ የመክፈል አቅም የሌላቸውን በራሳቸው ወጪ በማከም፣ መንገድ ላይ የወደቁትን በመኪናቸው ጭነው ወደ ቤትና ሕክምና በመውሰድ ያሳዩን ፍቅር በቃላት አይገለጽም።

​የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነትን ተቀብለው የኖሩና ሕይወታቸው ሲያልፍም በገዛ ፈቃዳቸው በደብረ ፀሐይ ቁስቋም ማርያም እንዲቀበሩ ተናዘው በማረፋቸው ድፍን የጎንደር ሕዝብ፦ "የማን ዘመድ ሞተ አትበለኝ ሀገሬ፣
ጎንደር ሰው ሞቷታል እናላቅሳት ዛሬ" ብሎ ማልቀሱ የሕዝብ ልጅነታቸውን ህያው ማረጋገጫ ነው።

​ዶክተር በርናርድ የሕክምና ምሁር ብቻ አልነበሩም፤ ዘመናዊ ቴክኒኮችን በመጠቀም ውስብስብ ቀዶ ጥገናዎችን በማከናወን ረገድ የተካኑና በዓለም አቀፍ ደረጃ በስማቸው የተመዘገቡ ሁለት የሕክምና መሣሪያዎች ፓተንት ያሏቸው ባለሙያ ነበሩ።

ከዚህም ባለፈ በእውቀት የተቃኘ የታሪክና የፍልስፍና ሰው፣ እውነተኛ የአፍሪካውያን አስተሳሰብ አምላኪ፣ "ሊምቢክ ግሊምፕስስ" (Limbic Glimpses) የተሰኘ የግጥም መድብልና የምርምር መጽሐፍ ያበረከቱ ደራሲ እንዲሁም አስደናቂ የስዕልና ቅርጻቅርጽ ችሎታ የነበራቸው ጥበበኛ ነበሩ።

​​የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የዚህን ታላቅ ሰው ውለታ ለመመለስ፦

1. ​በየዓመቱ በሥነ-ምግባራቸውና በሙያቸው ለተመሰከረላቸው ምርጥ የሕክምና ምሩቃን “የዶ/ር በርናርድ አንደርሰን ሽልማት” ይሰጣል።

2. የጎንደር ዩኒቨርሲቲ 70/100ዓመት ምሥረታ ባከበረበት ወቅት በሰፊው ከዘከራቸው መካከል አንዱ ሲሆኑ ​ለአስር ዓመታት ያስተማሩበትና ያገለገሉበት የቀዶ ሕክምና ማዕከል “የዶ/ር በርናርድ አንደርሰን ቀዶ ጥገና ማዕከል” ተብሎ በስማቸው ተሰይሟል።

​በእሳቸውና በባለቤታቸው ሲስተር እማዋይሽ መታሰቢያ የተሰየመው የሆስፒታሉ ክፍል "የዶክተር በርናርድ ዋርድ" ለታላቅ ቅርሳቸው ምስክር ሆኖ ያገለግላል።

​ከፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ በኋላም የዶ/ር በርናርድና የሲስተር እማዋይሽ መታሰቢያ ሙዚየም በታደሚዎች ተጎብኝቷል።

​ይህ ታሪካዊ ስምምነት የዶ/ር በርናርድና የሲስተር እማዋይሽ ገሪማ ራዕይና ትሩፋት ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲሻገር፣ ለኢትዮጵያ ዘላቂ የጤና አገልግሎት አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ወሳኝ እርምጃ ነው!
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
ሐምሌ 16 ቀን 2018ዓ.ም

History, a Lasting Legacy, and a Grand Vision Reach a New Chapter!

​The enduring vision of the honorable Dr. Bernard Anderson (affectionately known as “The Gondere of Jamaica”) and his life partner, Sister Emmawayish Gerima, who stood as towering role models of true love, noble philanthropy, and selfless devotion to country and community, has officially transitioned into a historic new chapter.

​The University of Gondar, alongside the legal heirs of Sister Emmawayish Gerima, the beneficiaries, and their trusted trustee, Ato Dawit Derbew, has signed a historic Memorandum of Understanding to fully complete the construction of the hospital and open its doors for public service.

​Beyond honoring the memory of these two great benefactors, this milestone brings multifaceted benefits to our nation's healthcare and education sectors:

​1. Sustainability and Safeguarding of a Precious Endowment

​By integrating the under-construction, modern 70-bed hospital and museum into the University of Gondar, the project will now be guided by a robust institutional and legal framework. This provides absolute assurance that the benefactors' legacy and endowment remain pristine, uncompromised, and uninterrupted, serving the public good for generations to come.

​2. Positioning Gondar as a Destination for Medical Tourism

​By expanding the specialized surgical disciplines initiated by Dr. Bernard during his lifetime, including hepatobiliary (liver), pancreatic, cardiovascular, and thoracic surgeries, the center will provide top-tier, high-quality medical services. This will draw patients not only from across Ethiopia but also from neighboring countries, establishing Gondar as a medical tourism hub and boosting the nation's foreign currency inflows.

​3. A Hub for Research and Academic Excellence

​This institution will serve as more than just a hospital; it will be a center of excellence providing high-quality postgraduate training and research opportunities for the next generation of physicians. This path will allow the unforgettable academic footprint Dr. Bernard left at our university to flourish even further.

​Who Was Dr. Bernard Anderson, "The Gondere of Jamaica"?

​Born in Jamaica in 1937, Dr. Bernard Anderson was a highly successful and prominent surgeon in Washington, D.C., USA. However, answering the profound call to "return to the pride of Black people, to the true land of humility," he moved to Ethiopia in 2005 G.C. to dedicate his entire life and wealth to the people of Gondar.

​An Icon of Love and Humility: Words cannot describe the love he showed—treating those who could not afford medical care at his own expense, and picking up the destitute from the streets in his own car to provide them with shelter and medical attention.

​A True Son of the People: Having embraced and lived the Ethiopian Orthodox Tewahedo faith, he willed to be laid to rest at the Debre Tsehay Kuskwam Mariam Church upon his passing. The grief of the entire population of Gondar, who wept chanting, "Ask me not whose relative has passed, my country; a giant of a man has died in Gondar, let us mourn him today," stands as living proof of how deeply he belonged to the community.

​A Man of Multifaceted Talents: Dr. Bernard was far more than a brilliant medical scholar. He was a master surgeon skilled in performing complex procedures using advanced techniques, holding international patents for two medical devices registered in his name. Beyond medicine, he was a deeply knowledgeable historian and philosopher, a true Pan-Africanist thinker, an author of research texts, a published poet who penned the collection “Limbic Glimpses,” and a gifted artist skilled in painting and sculpting.

​Repaying a Noble Debt: The Commitment of the University of Gondar

​To honor and preserve the immense contributions of this great man, the University of Gondar continues to strengthen its dedicated initiatives:

​The Dr. Bernard Anderson Award will be presented annually to outstanding medical graduates recognized for their exceptional ethics and professional excellence.

​Having been prominently honored during the University of Gondar's historic anniversary celebrations, the surgical center where he taught and served for a decade has been officially named “The Dr. Bernard Anderson Surgical Center” in his honor.

​The specific hospital unit named in memory of him and his spouse, “The Doctor Bernard Ward,” stands as a testament to their monumental legacy.
​(Following the signing ceremony, attendees also toured the Dr. Bernard and Sister Emmawayish Memorial Museum.)

​"This historic agreement is a decisive step that ensures the vision and legacy of Dr. Bernard and Sister Emmawayish Gerima are passed down from generation to generation, opening a brand-new chapter for sustainable healthcare in Ethiopia!"
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
​July 23, 2026

ባለፈው ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ‘ጽናት’ የተሰኘው መጽሐፌ በታሪካዊቷ ጎንደር ከተማ እጅግ በተዋበና በደመቀ ሥነ-ሥርዓት ተመርቋል። ጥሪያችንን አክብራችሁ፣ ከቅርብም ከሩቅም በመገኘት የ...
27/07/2026

ባለፈው ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ‘ጽናት’ የተሰኘው መጽሐፌ በታሪካዊቷ ጎንደር ከተማ እጅግ በተዋበና በደመቀ ሥነ-ሥርዓት ተመርቋል። ጥሪያችንን አክብራችሁ፣ ከቅርብም ከሩቅም በመገኘት የደስታችን ተካፋይ ለሆናችሁ ውድ እንግዶቻችን በሙሉ ያለኝን የከበረ ምስጋና እና አክብሮት ለመግለጽ እወዳለሁ።

​ይህ መጽሐፍ የአንድ ግለሰብ ታሪክ ሳይሆን፤ የታላቁ ተቋማችን የጎንደር ዩኒቨርሲቲን የ70 ዓመታት ተቋማዊ ጉዞ፣ የማህበረሰባችንን ታላቅ ተጋድሎ እና የሀገራችንን የከፍተኛ ትምህርት ታሪክ ውጣ ውረዶችና ስኬቶች በ11 ምዕራፎች አዋቅሮ የያዘ የጋራ ማህደራችን ነው።

​ይህንን መጽሐፍ ለማዘጋጀት ስነሳ የነበረኝ ዋነኛ ተስፋና ዓላማ፦

​ለተቋማችን ታሪክ ቀጣይ ጥናቶችና ምርምሮች ጠንካራ መነሻ ለማስቀመጥ፣
​በአመራሮቻችን ዘንድ ተቋማዊ ታሪክንና ተሞክሮን የመሰነድ ባህል እንዲጎለብት ለማበረታታት፣
​በተለይም ደግሞ ለቀጣዩ ትውልድ ወጣት መሪዎች አስቸጋሪ ሁኔታዎችን በጽናት አልፈው የሚጓዙበትን ፍኖተ-ካርታ ለማሳየት ነው።
​የአመራርነት ጉዞ የኃላፊነት ውጥረት የበዛበት ቢሆንም፣ በተግባር ያካበትነውን ጥልቅ ዕውቀት፣ ያጋጠሙንን ፈተናዎችና የተማርናቸውን ልምዶች ለተተኪው ትውልድ በብዕር ማውረስ ተቋማዊ ቀጣይነትን ለማረጋገጥ ትልቁ አደራችን ነው ብዬ አምናለሁ።

የዚህ መጽሐፍ የመጀመሪያ እትም ሽያጭ 50 በመቶ (50%) ለተቸገሩ ሕጻናት ተማሪዎች የ2019 የትምህርት ዘመን የትምህርት ቁሳቁስ ማሟያ የሚበረከት መሆኑን በታላቅ ደስታና በትህትና እገልጻለሁ።

​ይህ መጽሐፍ ከሐሳብ ደረጃ ጀምሮ ዛሬ እጃችሁ ላይ እስኪደርስ ድረስ፦

ያለሰለሰ ድጋፍ ላደረጉልኝ ውድ ወዳጆቼና ቤተሰቦቼ፣ ረቂቁን በሳይንሳዊ ዕይታ ለገመገሙ ምሁራን፣ ሁልጊዜም የጽናታችን ምንጭ ለሆነው ለመላው የጎንደር ከተማ ሕዝብ፣ ለጎንደር ከተማና ለማዕከላዊ ጎንደር ዞን አስተዳደር አመራሮች፣ ለኤቢ ኢንተርቴይመንትና ኢቨንት፣ ለጎንደር ባህል ማዕከል፣ ለዩኒቨርሲቲያችን የሙዚቃ ትምህርት ክፍል፣ ለታዳጊውና ባለብሩህ አእምሮው ተማሪ አዛርያስ ፋሲል፣ ለመላው የዩኒቨርሲቲያችን ማሕበረሰብ አባላት፣ በስኬቶቻችንም ሆነ በአስቸጋሪ የሥራ ወቅቶች ከጎኔ ላልተለዩኝ ውድ የሥራ ባልደረቦቼ፣ ፋሲል ከነማ ደጋፊዎች ማህበር፣ እንዲሁም ይህ የምረቃ ፕሮግራም በአጭር ጊዜ ውስጥ በጥራት እንዲዘጋጅ ሌሊት ከቀን ለደከሙት የአዘጋጅ ኮሚቴ አባላት በሙሉ የምስጋናዬ አድማስ የላቀ ነው።

​‘ጽናት’ ለእናንተ ለውድ አንባቢዎች ተበርክታለች። ታሪካችንን እያነበብን፣ በገንቢ ሂስና በውይይት ዕውቀታችንን የምናሳድግበት ይሆን ዘንድ መልካም ንባብ እመኛለሁ!

​በድጋሚ ከልብ አመሰግናለሁ!

፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
ሐምሌ 20 ቀን 2018 ዓ.ም

"ጽናት" የተሰኘው መጽሐፍ የሽፋን ስዕል ትርጉም!፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥​የ"ጽናት" መጽሐፍ የሽፋን ስዕል የተቋማችንን ያለፈ ታሪክ፣ የአሁኑን ጥ...
26/07/2026

"ጽናት" የተሰኘው መጽሐፍ የሽፋን ስዕል ትርጉም!
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥

​የ"ጽናት" መጽሐፍ የሽፋን ስዕል የተቋማችንን ያለፈ ታሪክ፣ የአሁኑን ጥንካሬ እና የወደፊቱን ብሩህ ተስፋ በምስል የሚተርክ ነው።

የሽፋኑ ዋና ዋና ምስሎች ትርጓሜ እንደሚከተለው ቀርቧል፦
​ሀ- ያረጀው ግን ህያውና ፍሬያማው ዋርካ፦

የመጽሐፉን ሽፋን የተመለከተ ሰው ከታች ከተሰነጣጠቁ ግን ጠንካራ የድንጋይ መሠረቶች ላይ የበቀለ፣ ያረጀ ግን ህያውና ፍሬያማ የ‘ዋርካ’ ዛፍ ያያል። ይህ ዛፍ በአንድ በኩል የታሪካዊቷን ጎንደር ከተማ መለያ የሆነውን "ጃንተከል ዋርካን" ሲወክል፤ በሌላ መልኩ ደግሞ የዩኒቨርሲቲያችንን የ70 ዓመታት እና የሆስፒታላችንን የምዕተ-ዓመት ጉዞ፣ እሾህና አሜኬላውን ሁሉ በጽናት አልፎ ዛሬም ድረስ አረንጓዴና ፍሬያማ ሆኖ መቆሙን ያሳያል።

​ለ- የፋሲለደስ አብያተ መንግሥታት (በግራ በኩል)፦

ይህ በግራ በኩል በግርማ ሞገስ የሚታየው ታሪካዊ ቅርስ የመጣንበትን ጥንካሬ፣ ታሪካዊ መነሻችንን እና ለአሁኑ ማንነታችን መሠረት የሆነውን የሊቃውንትና የጥበብ ምድር ጎንደርን ይወክላል።

​ሐ- የዩኒቨርሲቲው መግቢያ በርና የፀሐይ ብርሃን (በቀኝ በኩል)፦

በቀኝ በኩል ያለው የዩኒቨርሲቲው ዋና መግቢያ በር ከውስጥ ወደ ውጭ የሚፈነጥቀውን የእውቀት ብርሃን የሚያሳይ ሲሆን፤ ከበሩ ማዶ የሚታየው የደመቀው የፀሐይ ብርሃን ደግሞ የተቋማችንን ብሩህ የወደፊት ተስፋና ጉዞ ያበስራል።

​መ- ሰማያዊው የሰማይ ዳራ (በላይኛው በኩል)፦
በላይኛው በኩል የሚታየው ሰማያዊ ቀለም የተቋማችንን የሰላም እሴት፣ የአካዳሚክ ልዕልናን እና የራዕያችንን ታላቅ ስፋትና ጥልቀት ያመለክታል።

​"ጽናት — የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ታሪካዊ የለውጥ ጉዞ (1947 - 2017 ዓ.ም.)"

​ይህ መጽሐፍ የትናንቱን ውጣ ውረድ፣ የዛሬውን ስኬትና የነገውን ራዕይ የምንቃኝበት መስታዎታችን ነው።

​መልካም ንባብ!
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
ሐምሌ 19 ቀን 2018ዓ.ም

The Symbolism Behind the Book Cover of "Tsinat" (Resilience)!

​The cover art of the book "Tsinat" (Resilience) visually narrates our institution's past history, present strength, and bright future.

​The interpretation of the main imagery on the cover is presented below:

​A. The Ancient, Yet Alive and Fruitful Warka (Banyan) Tree:

​Anyone looking at the book cover will see an ancient, yet vibrant and fruitful 'Warka' tree growing from cracked but solid stone foundations below. On one hand, this tree represents the "Jantekel Warka," a historic symbol of Gondar city.

On the other hand, it symbolizes the 70-year journey of our university and the century-long history of our hospital, demonstrating how they have overcome every thorn and obstacle with resilience, remaining green and productive to this day.

​B. The Fasilides Castles (On the Left):

​This historical heritage visible in its full majesty on the left represents our strong roots, our historical origins, and Gondar, the land of scholars and wisdom, which serves as the foundation for our current identity.

​C. The University Gates and the Sunlight (On the Right):

​The university's main entrance on the right illustrates the light of knowledge radiating from within to the outside world. Meanwhile, the bright sunlight gleaming beyond the gate heralds the bright future and upcoming journey of our institution.

D. The Blue Sky Background (At the Top):
The blue color stretching across the upper part of the cover symbolizes our commitment to peace, academic excellence, and the vast, limitless horizon of our institutional vision.

​"Resilience — The Historical Journey of Transformation of the University of Gondar (1954 - 2025 G.C."

​This book is our mirror, a reflection through which we examine yesterday's ups and downs, today's achievements, and tomorrow's vision.
​Happy Reading!

፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
​July 25, 2026

ጽናት፡ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ታሪካዊ የለውጥ ጉዞ!Resilience: The University of Gondar's Historic Journey of Transformation!
24/07/2026

ጽናት፡ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ታሪካዊ የለውጥ ጉዞ!

Resilience: The University of Gondar's Historic Journey of Transformation!

የጎንደር ዩኒቨርሲቲን ዓለምአቀፋዊ ትስስር ይበልጥ ወደላቀ ደረጃ ያሸጋገረውን ታሪካዊ ክንውን ለእናንተ ስናካፍል በታላቅ ደስታ ነው።​በቅርቡ በሌስተር ዩኒቨርሲቲ ባደረግነው ጉብኝት፣ ላለፉት ...
22/07/2026

የጎንደር ዩኒቨርሲቲን ዓለምአቀፋዊ ትስስር ይበልጥ ወደላቀ ደረጃ ያሸጋገረውን ታሪካዊ ክንውን ለእናንተ ስናካፍል በታላቅ ደስታ ነው።

​በቅርቡ በሌስተር ዩኒቨርሲቲ ባደረግነው ጉብኝት፣ ላለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት ገደማ እያደገ የመጣውን የሁለትዮሽ ግንኙነታችንን በድጋሚ ያረጋገጠውን የመግባቢያ ስምምነት በታላቅ ኩራት አድሰናል። በጋራ በመሆንም፣ በምርምር፣ በአካዳሚክ አቅም ግንባታ፣ በአመራር ልማት እንዲሁም የጋራ የሆኑ ዓለምአቀፍ ፈተናዎችን ለመፍታት በሚረዱ የፈጠራ ሥራዎች ዙሪያ ያለንን ትብብር ይበልጥ እያጠናከርን እንገኛለን።

​ለፕሮፌሰር ሰር ኒሻን ካናጋራጃህ፣ ለፕሮፌሰር ሪቻርድ ቶማስ እና ለመላው የሌስተር ዩኒቨርሲቲ የሥራ ባልደረቦች ላደረጉልን ሞቅ ያለ አቀባበል እና ለዚህ ዘላቂ አጋርነት ላሳዩት የማይናወጥ ቁርጠኝነት ያለኝን ከልብ የመነጨ ምስጋና አቀርባለሁ።

​በቀጣይም ለተቋማቶቻችን፣ ለአገራችን እና ለዓለምአቀፉ የአካዳሚክ ማኅበረሰብ የላቀ እና ትርጉም ያለው ተፅዕኖ ለመፍጠር በጋራ ለመሥራት እንተጋለን።

​ለበለጠ መረጃ፡

"University of Leicester – Leicester renews landmark Ethiopia partnership after three decades of collaboration" ( https://le.ac.uk/news/2026/may/gondar-leicester-university-ethiopia-delegation )
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም.


I'm delighted to share the important milestone in the internationalization journey of the University of Gondar.

During our recent visit to the University of Leicester, we proudly renewed our Memorandum of Understanding, reaffirming a partnership that has flourished for nearly three decades. Together, we're strengthening collaboration in research, academic capacity building, leadership development, and innovation to address shared global challenges.

My sincere appreciation goes to Professor Sir Nishan Canagarajah, Professor Richard Thomas, and the entire University of Leicester team for their warm hospitality and unwavering commitment to this enduring partnership.

Together, we look forward to creating greater impact for our institutions, our communities, and the global academic community.

Read more:

"University of Leicester – Leicester renews landmark Ethiopia partnership after three decades of collaboration" ( https://le.ac.uk/news/2026/may/gondar-leicester-university-ethiopia-delegation)
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
July 22, 2026
Ministry of Education Ethiopia Aynishet Adane Lijalem Gashaw Ministry of Education Ethiopia Medical Information Ministry of Health,Ethiopia Binyam C. Tilahun

University of Leicester has renewed its landmark partnership with the University of Gondar, building on nearly three decades of collaboration in research, education and capacity building.

Address

Addis Ababa Science And Technology University
Gondar
P.O.BOX16417

Opening Hours

Monday 08:00 - 17:00
Tuesday 08:00 - 17:00
Wednesday 08:00 - 17:00
Thursday 08:00 - 17:00
Friday 08:00 - 17:00

Telephone

+251581141231

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Asrat Atsedeweyn posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The University

Send a message to Asrat Atsedeweyn:

Shortcuts

Share