Wachemo University WCU ETH

Wachemo University WCU ETH Let your light shine in the society!

የቀይ እንባ ወተትየዋቸሞ ዩኒቨርስቲ መምህርና ተመራማሪ የሆኑት መምህር ምስጋና ተመስገን በህገወጥ ስደት እና አስከፊነት ላይ የተመሠረተ "Kashar "Indiixxi Ado" "የቀይ እንባ ወተ...
05/09/2025

የቀይ እንባ ወተት
የዋቸሞ ዩኒቨርስቲ መምህርና ተመራማሪ የሆኑት መምህር ምስጋና ተመስገን በህገወጥ ስደት እና አስከፊነት ላይ የተመሠረተ "Kashar "Indiixxi Ado" "የቀይ እንባ ወተት" በሚል ርዕስ በሀዲይሳና በአማርኛ ቋንቋ የተጻፈው የገሐዱ ዓለም ነጸብራቅ የሆነው መጽሐፍ በዘሬው ዕለት በቪክቲሪ ሆቴል የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባል፣ የዞን ም/ቤት አባላት፣ የዞን መምሪያ ኃላፊዎች፣ የወረዳ አስተዳዳሪዎች ነጋዴዎች፣ የዩኒቨርስቲው ምሁራንና የሐዲይሳ ቋንቋ ትምህርት ክፍል ተማሪዎች የደራሲው ቤተሰቦች እና ሌሎች እንግዶች በተገኙበት ተመርቋል።
እኔም በመጽሐፉ የአማርኛው እትም ላይ በተወሰነ ደረጃ ተሳትፎ ያደረኩት በመሆኑ በምረቃው ሥርዓት በመታደሜ በእጅጉ ደስ ብሎኛል።

05/09/2025
22/08/2025

07/07/2025
በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ዱራሜ ካምፓስ ለ10ኛ ዙር በመደበኛና በተከታታይ ትምህርት ክፍሎች ያሰለጠናቸውን  161 ተማሪዎችን በዛሬው እለት በድምቀት እያስመረቀ ነው።በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ዱራሜ ካምፓስ...
22/06/2025

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ዱራሜ ካምፓስ ለ10ኛ ዙር በመደበኛና በተከታታይ ትምህርት ክፍሎች ያሰለጠናቸውን 161 ተማሪዎችን በዛሬው እለት በድምቀት እያስመረቀ ነው።

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ዱራሜ ካምፓስ ለ10ኛ ዙር በመጀመሪያ ድግሪ በመደበኛ ትምህርት መርሃ ግብር በኢንጅነርንግና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ በሁለት ትምህርት ክፍሎች ያሰለጠናቸውን 161 ተማሪዎች በዛሬው እለት በድምቀት እያስመረቀ ይገኛል።

በምረቃ መርሃግብሩ የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪና የእለቱ ክቡር እንግዳ የተከበሩ አቶ አረጋ እሸቱ፣ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ዳዊት ሃዬሶ፣ የከምባታ ዞን ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ አስካለ ሰሶ፣ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ዱራሜ ካምፓስ ችፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይረክተር ረዳት ፕሮፈሰር ዘውዴ ክፍሌን ጨምሮ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት፣ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የሴኔት አባላት ፣ ተመራቂ ተማሪ ቤተሰቦችና ሌሎችም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

የሰላም አምባሳደር የሆነችው ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የምረቃ በዓሉን ደማቅ የሚያደርጉ የቅድመ ዝግጅት ሁኔታዎች ተጠናቀዋል።ወድ ተመራቂ ተማሪዎችና ቤተሰቦች እንዲሁም እንግዶቻችን ከወዲሁ እንኳን አደ...
20/06/2025

የሰላም አምባሳደር የሆነችው ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የምረቃ በዓሉን ደማቅ የሚያደርጉ የቅድመ ዝግጅት ሁኔታዎች ተጠናቀዋል።

ወድ ተመራቂ ተማሪዎችና ቤተሰቦች እንዲሁም እንግዶቻችን ከወዲሁ እንኳን አደረሳችሁ።

ዩኒቨርሲቲው በነገው ዕለት ሰኔ 14/2017ዓ/ም በደማቅ ስነ-ስርዓት 1255 ተማሪዎች ይመረቃሉ።

እንኳን ደስ አላችሁ!

Let Your Light Shine in the Society!

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ከሰኔ 02-10/2017 ዓ.ም የተሰጠው ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና በስኬት ተጠናቀቀ።በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ከሰኔ 02-10/2017 ዓ.ም  የተሰጠው የቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች እና...
17/06/2025

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ከሰኔ 02-10/2017 ዓ.ም የተሰጠው ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና በስኬት ተጠናቀቀ።

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ከሰኔ 02-10/2017 ዓ.ም የተሰጠው የቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች እና ከዲፕሎማ ወደ ድግሪ ደረጀ ማሻሸያ ለሚያደርጉ መምህራን የተሰጠው ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና በሰላምና በስኬት ተጠናቅቋል።

ፈተና በስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዳዊት ሃዬሶ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ፕሬዝዳንቱ በመልዕክታቸው፥ ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና በሰላም እንዲጠነቀቅ የጋራ ትብብር ድምር ውጤት መሆኑን ገልጸዋል።

ለፈተና ስኬት የራሳቸውን ድርሻ ላበረከቱ አካላት በተለይም ለዩኒቨርሲቲያችን የፈተና ግብረሃይል፣ የፌዴራል ፖሊስ፣ ለግቢ ደህንነት፣ ለኢኮቴ ዘርፍ፣ ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ፣ ለሌሎች ባለድርሻ አካላት ላቅ ያለ ልባዊ ምስጋና አቅርበዋል።

ሰኔ 10/2017 ዓ.ም

ዘገባው የህዝብ ግንኙነት እና ዓለም ዓቀፍ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።

Let Your Light Shine in the Society!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፣
ድረ ገጽ:- www.wcu.edu.et
ፌስቡክ:-Wachemo University-WCU
Telegram channel-https://t.me/Wcuniversity
YouTube-Wachemo University-wcu youtube
P.O.Box 667

09/06/2025

የ2017 ዓ.ም የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና መሰጠት ጀመረ፤
------------------------------------
(ሰኔ 02/2017 ዓ.ም) በዩኒቨርስቲዎች የሚሰጠው የቅድመ ምረቃ የመውጫ ፈተና ከዛሬ ጀምሮ እስከ ሰኔ 10/2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።

የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) እንደገለጹት ፈተናው የሚሰጠው በ51 ዩኒቨርስቲዎች በተዘጋጁ 87 የፈተና ማዕከላት ነው።

በዚህ ዓመት በሚሰጠው የመውጫ ፈተና 190,787 ቅድመ መደበኛ እጩ ተመራቂ ተማሪዎች ፈተናውን እንደሚወስዱ እና ከዚህም ውስጥ 102 ሺ 360 ተማሪዎች ፈተናውን ለመጀመሪያ ጊዜ የሚወስዱ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

ፈተናው በ238 የትምህርት መርሃ ግብሮች በሁሉም የፈተና መስጫ ማዕከላት በበይነ መረብ እንደሚሰጥም ዶ/ር ኤባ ጨምረው ገልጸዋል።

Address

Ambicho
Hossana
TEME

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wachemo University WCU ETH posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The University

Send a message to Wachemo University WCU ETH:

Share