22/09/2025
የትምህርት ጉዳይ የሁላችንም ጉዳይ ነዉ !!
ህጻናት ይማሩ!
የአንድ ሀገር ሁለንተናዊ እድገት እና ብልጽግና ማምጣት የሕዝቦቿን ኑሮ ማሳደግ የሚቻለው በሚኖራት የተማረ የሰው ኃይል እምቅ አቅም ነዉ።
እንደሀገር ለመጽናት እንደ ህዝብ ለመኖርም ትምህርት ላይ መስራት ብቸኛዉ መዉጫ መንገድ መሆኑ ሀቅ ነዉ።
ትምህርት ዘላቂ የአስተሳሰብ ለውጥን በማምጣት ፣ የአንድን ሀገር ሰላም፣ እድገትና ብልጽግና በማረጋገጥ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ በመሆኑ ከቤተሰብ ጀምሮ ማህበረሰቡ በጋራ መስራት ይኖርበታል።
በክልላችን ሁሉም እድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህፃናትና ወጣቶች ወደ ትምህርት ተቋማት እንዲገቡና ያለአንዳች የጊዜ ብክነት ማግኘት ያለባቸውን የትምህርት ፍሬ እንዲያገኙ ማስቻል ይጠበቅብናል።
በዚህ ረገድ በትምህርት ዘመኑ ያለው አጀማመር ካለፉት ጊዜያት ለውጦች ቢኖሩትም አሁንም ፈጣን ጥረትና እገዛ ከሁላችንም ይጠበቃል።
!
!
!
!
🕊ሰላም ለሁሉም፤ ሁሉም ለሰላም🕊
•~•~•
"የጎርጎራ ቃልኪዳናችን፤ ለዘላቂ ሰላም እና ለሁለንተናዊ ብልጽግናችን"
•~•~