Kibrit Getie

Kibrit Getie Gebeze mariym

23/02/2023

[የእመቤታችን የየካቲት 16 ቃል ኪዳኗን አስመልክቶ በሊቃውንት የቀረበላት ውዳሴ (ቅዱስ ያሬድ፣ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ፣ አባ ዘመለኮት፣ አባ ጽጌ ድንግል)]
✍️ አዘጋጅ፡- መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
💥 ቅዱሳን ሊቃውንት የአምላክን እናት አመስግነው በቃኝ አይሉም ነበር በተለይ ከኢትዮጵያ ሊቃውንት ቅዱስ ያሬድ፣ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ፣ አባ ጽጌ ድንግልና አባ ዘመለኮትን በዚህ ክፍል ላይ ስጠቅሳቸው በተለይ የክብር ባለቤት ልጇ በጎልጎታ የምሕረት ቃል ኪዳንን የገባላትን የየካቲት 16 ክብረ በዓሏን አስመልክቶ ከጻፉት ከብዙው በጣም ጥቂቱን የእመቤቴን በረከት ለመሳተፍ ስል አስፍሬዋለሁ፡፡
💥በቅዱስ ያሬድ💥
❤ ቅዱስ ያሬድ በድጓው በተለይ በዐጫብር ድጓ ዘኪዳነ ምሕረት ውስጥ ከተጻፈው፡-
✍️ “ለብእሲ ዕሩቅ እምልብሰ ምግባር
ታዕድዊዮ እምገሃነም ባሕር
ኦ ድንግል በኪዳንኪ ሐመር”

(ድንግል ሆይ በቃል ኪዳንሽ መርከብ ከምግባር ልብስ የተራቈተውን ሰው ከገሃነመ እሳት ባሕር ታሻግሪዋለሽ)

✍️ “ብእሲ ቅሩብ ለሙስና
ለድንግል በኪዳና
በመንግሥተ ሰማይ ዘኢይጸልም ብርሃና
ይረክብ ሕይወተ ዕረፍት ወጥዒና”

(ለጥፋት የቀረበ ሰው ለድንግል በተሰጣት ኪዳን፤ ብርሃኗ በማይጨልም በመንግሥተ ሰማይ ዕረፍትና ጤንነትን ያገኛል)

✍️ “ክነፈ ርግብ በብሩር ዘግቡር ወገበዋቲሃኒ በሐመልማለ ወርቅ
አንቲ ምሥራቅ ወወልድኪ ፀሐየ ጽድቅ
አማን ኪዳንኪ ኢየሐልቅ”

(በብር የተሠራች የርግብ ክንፍ ጐኖቿ በወርቅ ዐመልማሎ የተሸለመች አንቺ በምሥራቅ ስትመሰዪ ልጅሽ የእውነት ፀሐይ ነው፡፡ በእውነት ቃል ኪዳንሽ አያልቅም)፡፡

✍️ “አዕረግዋ መላእክት እምድር ውስተ ሰማያት በክብር ወበስብሐት
በእንቲኣነ ከመ ትስአል እምወልዳ ኪዳነ ምሕረት”

(ስለ እኛ ከልጇ የምሕረት ኪዳንን ትለምን ዘንድ በክብር በምስጋና መላእክት ከምድር ወደ ሰማያት አሳረጓት፡፡)

✍️ “ይቤላ ለእሙ ማርያም እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ተካየድኩ ምስሌኪ ኪዳነ ምሕረት ከመ አድኅን ዘተአመነኪ መሐልኩ ለኪ በርእስየ ዘመሐልኩ አነ ለኖኅ ገብርየ ወለአብርሃም ፍቁርየ፤ ዘመሐልኩ አነ ለዳዊት ኅሩይየ ብእሲ ምእመን ዘከመ ልብየ መሐልኩ ለኪ በርእስየ በቅዱስ ሥጋየ ወበክቡር ደምየ መሐልኩ ለኪ በርእስየ ከመ ኢይሔሱ ማእኰትየ”

(ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ ማርያምን እንዲኽ አላት በምልጃሽ ያመነብሽን አድን ዘንድ ካንቺ ጋራ የምሕረት ቃል ኪዳንን ተጋባኊ፤ ለአገልጋዬ ለኖኅና ለወዳጄ ለአብርሃም ቃል የገባኊ እኔ በራሴ ማልኹልሽ፤ እንደ ልቤ ለምለው ለታመነው ለዳዊት የማልኊ እኔ በራሴ ማልኹልሽ፤ በቅዱስ ሥጋዬና በክቡር ደሜ የማልኊ እኔ ምዬ እንደማልከዳ ማልኹልሽ)
💥💥💥

💥 አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ💥
✍️ድካመ ጌጋይየ ትማእ ማርያም ጽድቀ ዚኣኪ በጽንዓ
መዳልወ ጥበብ ሶበ መልኣ ሰማኒተ ነፍሳተ ወሰብዓ
ሕፍነ ማይ ኀየለ ወሞአ”

(ማርያም የአንቺ ጽድቅ የበደሌን ድካም ድል ትነሣ ዘንድ የጥበብ (የምስጢር) ሚዛኖች በመሉ ጊዜ እፍኝ ውሃ ሰባ ስምንት ነፍሳትን ፈጽሞ ድል ነሣ፡፡)

✍️ “በከመ ልማድኪ በሊ ኀበ ወልድኪ ከሃሊ
ኦ ርኅሩኅ ኢተበቃሊ
ያጠፍኦኑ ለሥዕሉ ሠዓሊ
ኪነተከ ዘትካት ኀሊ”

(እንደ ልማድሽ ኹሉን የሚችል ወደሚኾን ልጅሽ የማትበቀል ቸር ሆይ፤ ሠዓሊ ሥዕሉን ያጠፋዋልን? የቀድሞ ፍጥረትኽን ዐስብ በዪ)።

✍️ “ጊዜ ጸልዮትኪ በጽሐ ከመ ኢይሙት ገብርኪ
ቅድሜሁ ስግዲ ወአስተብርኪ
እንዘ ታዘክሪዮ እምጻማ ንግደትኪ
ርግብየ የዋሂት ለየዋህ ወልድኪ”

(ደገኛዪቱ ርግቤ ለደገኛው ልጅሽ የእንግድነትሽን ድካም እንደ እናት እያሳሰብሺው፤ በፊቱ ፍጹም ስገጂ፤ አገልጋዪሽ እንዳይሞት የጸሎትሽ ጊዜ ደረሰ)።

✍️ “እሙ በሊዮ በእንቲኣየ ለፍሬ ከርሥኪ እብኖዲ
ላዕሌሁ ምሕረተ ኢታጐንዲ
እመ አሕዘነከ ብእሲ አባዲ
ቤዛ ነፍሱ ንጽሕየ እፈዲ”

(የጌታዬ እናት የማሕፀንሽ ፍሬ እብኖዲን ስለ እኔ እንዲኽ በዪው በርሱ ላይ ይቅርታን አታዘግዪ፤ ሰነፍ ሰው ቢያሳዝንኽም የነፍሱን ምትክ ንጽሕናዬን ዋጋ አድርጌ እከፍልለታለኊ)።

✍️ “አንቲ ውእቱ ለእግዚአብሔር አትሮኑሱ
ለአዳም ክብረ ሞገሱ
በኪዳንኪ ኃጥኣን መንግሥተ ሰማያት ይወርሱ"

(የእግዚአብሔር አትሮንሱ (ዙፋኑ) የአዳም የግርማው ክብር አንቺ ነሽ፤ ኃጥኣንም በቃል ኪዳንሽ መንግሥተ ሰማያትን ይወርሳሉ)።

💥💥💥

💥 አባ ጽጌ ድንግል 💥
✍️ “ሚ ሠናይ ከመ ጼና ጽጌ ልሑይ
በኲሉ ጊዜ ምሒረ ነዳይ
በእንተ ኪዳንኪ ድንግል ለበላዔ ሰብእ ጊጉይ
ሶበ ዐብየ እምኀጢአቱ ክበደ መድሎቱ ለማይ
ለተአምርኪ በሰማይ ተገብረ ግናይ”

(ኹል ጊዜ ለደኻ መራራት መመጽወት እንደ ለመለመ አበባ ያማረ ነው (ምን ያምር?) ድንግል በቃል ኪዳንሽ ምክንያት ከበላዔ ሰብእ ኀጢአት የውሃ ሚዛን በልጦ በመታየቱ ለተአምርሽ በሰማይ ምስጋና ኾነ)።

✍️ “በከመ ይቤ መጽሐፍ ማእከለ ፈጣሪ ወፍጡራን
ለዕረፍት ዘኮንኪ ትእምርተ ኪዳን
ሰንበተ ሰንበታት ማርያም ዕለተ ብርሃን
ብኪ ይትፌሥሑ ዘገነተ ጽጌ ጻድቃን
ወብኪ ይወጽኡ ኃጥኣን እምደይን”

(መጽሐፍ እንደተናገረ በፈጣሪና በፍጡራን መካከል ለዕረፍት የኪዳን ምልክት የሆንሽ የብርሃን ዕለት የሰንበታት ሰንበት ማርያም በአንቺ የገነት አበባ ጻድቃን ይደሰታሉ፡፡ ኃጥአንም በአንቺ ምልጃ ከሲኦል ይወጣሉ)፡፡

💥💥💥
💥የመልክአ ኪዳነ ምሕረት ደራሲ አባ ዘመለኮት💥
✍️ “ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘአስተማሰልዎ በኮከብ
ሶበ ብርሃኖ ተከድኑ ጽልሙታነ ራእይ ሕዝብ
ኪዳነ አምላክ ማርያም ወተስፋ መድኀኒት ዘዐርብ
ተናዘዘ ብኪ አኮኑ ኅሊና ቀዳማይ አብ
አመ እምገነቱ ተሰደ በሐዘን ዕጹብ”

(ለጨለመባቸው ወገኖች ብርሃኑን ባሳየ ጊዜ በኮከብ የመሰሉት ለኾነ ለስም አጠራርሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ የዐርብ የመድኀኒት ተስፋ የአምላክ ኪዳን ማርያም ሆይ በሚያስጨንቅ ሐዘን ከገነቱ በተሰደደ ጊዜ የመዠመሪያው ሰው ኅሊና ባንቺ ተረጋጋብሽ እኮን)።

✍️ “ሰላም ለአእዛንኪ እለ ተበሥራ ኪዳነ
እምአፈ ፈጣሪ ወልድኪ ዘባሕርየኪ ተከድነ
አምሕለኪ ማርያም ከመ ኢታርእዪኒ ደይነ
እንበለ ምግባር ባሕቱ እመ ኢይጸድቅ አነ
ቦኑ ለከንቱ ኪዳንኪ ኮነ”

(ባሕርይሽን ከተዋሐደ ከፈጣሪ ልጅሽ አንደበት የኪዳን ምሥራችን ለተበሠሩ ጆሮዎችሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ ያለምግባር የማልጸድቅማ ከኾነ በውኑ ኪዳንሽ ለከንቱ ይኾናልና ማርያም ሆይ ፍርድን እንዳታሳዪኝ አምልሻለኊ)።

✍️ “ማርያም ኅሪት እምነ መላእክት ወሰብእ
ተዝካረኪ ለእመ ገብረ በተአምኖ ጽኑዕ
በመንግሥተ ሰማይ ምስሌኪ ይነግሥ ኃጥእ”

(ከመላእክትና ከሰዎች ይልቅ የተመረጠሸ ማርያም ሆይ መታሰቢያሽን በብርቱ መታመን ያደረገ በመንግሥተ ሰማይ ካንቺ ጋር ይነግሣል) በማለት አወድሰዋታል፡፡

💥 እኛም በረከቷ ይደርብን ጸሎቷ ይጠብቀን፡፡
✍️ መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ

19/01/2023
19/01/2023
ደብረ ማርያም ገዳም
02/12/2022

ደብረ ማርያም ገዳም

02/11/2022
መጥቅቴ ቢበዛ አበቅቴ ቢያንስ ከ30 አይበዙም አያንሱም” ይህም ማለት በሌላ አገላለጽ መጥቅዕና አብቅቴ ተደምረዉ ዉጤቱ ከ30 መብለጥና ማነስ የለበትም፤ ሁሌ 30 ይሆናል፡፡ የዘንድሮዉ ~የ20...
12/09/2022

መጥቅቴ ቢበዛ አበቅቴ ቢያንስ ከ30 አይበዙም አያንሱም” ይህም ማለት በሌላ አገላለጽ መጥቅዕና አብቅቴ ተደምረዉ ዉጤቱ ከ30 መብለጥና ማነስ የለበትም፤ ሁሌ 30 ይሆናል፡፡ የዘንድሮዉ ~የ2015 ዓ.ም = 21+9= 30
✍.መጥቅዕ ከ14 በላይ ከሆነ በታህታይ ቀመር በመስከረም ይውላል።
✍.መጥቅዕ ከ14 በታች ከሆነ በላዕላይ ቀመር በጥቅምት ይዉላል።
~መጥቅዕ በመስከረም ቢዉል ጾመ ነነዌ በጥር፣ መጥቅዕ በጥቅምት ቢዉል ጾመ ነነዌ በየካቲት ይብታል።
ስለዚህ በዚህ ዓመት መጥቅዕ 21 ሲሆን ከ14 ይበልጣል፤ ስለዚህም መጥቅዕ በጥር ይዉላል።
ስለዚህ የ2015 መጥቅዕ ጥር 29 ነው ሲሆን ዕለተ መጥቅዕ ሰኛ ይሆናል፡፡
መባጅ ሐመር
~ ተዉሳክ በ2 ይከፈላል ።
~ የእለት ተዉሳክ
~ አጽዋማትና የበዓላት ተዉሳክ ተብለዉ ።
📚.የዕለት ተውሳክ ከቅዳሜ ይጀምራል፡፡
• ቅዳሜ=8
• እሁድ=7
• ሰኞ=6
• ማግሰኞ=5
• ረቡዕ=4
• ሐሙስ=3
• ዓርብ=2
📚.የአጽዋማትና የበዓላት ተውሳክ ከነነዊ ይጀምራል፡፡
~ ነነዊ የዕለት ተዉሳክ የለዉም ።
~ ዓብይ ፆም =14
~ ደብረ ዘይት =11
~ ሆሳዕና =2
~ ስቅለት =7
~ ትንሳኤ =9
~ ርክበ ካህናት =3
~ ዕርገት =8
~ ጰራቅልጦስ =8
~ ፆመ ድህነት =1
~ ፆመ ሐዋርያ =9
መባጃ ሐመርን ለማግኘት መጥቅዕንና በዓለ መጥቅዕ የዋለበትን ዕለት ተውሳክ መደመር ነው።
~ ነነዊ = መጥቅዕ + የዕለት ተዉሳክ
በዓለ መጥቅዕ የዋለው መስከረም ላይ ሆኖ ቅዳሜ ስለሆነ የቅዳሜ ተውሳክ 8 ነው።
መባጃ ሐመር= 21+8=29
መባጃ ሐመር ከ30 ስለሚያንስ ራሱ 29 ይያዝና መጥቅዕ በጥር ስለዋለ ጾመ ነነዌ በጥር 29 በዕለተ ሰኞ ይውላል ማለት ነው።
~ጾመ ነነዌ ተውሳክ የለውም በመባጅ ሐመር ይወጣል።ስለዚህ ጾመ ነነዌ በጥር 29 ይውላል።
ከዚህ ተነስተን አጽዋማትንና በዓላትን ተውሳኮቻቸውን ከመባጅ ሐመር ጋር እየደመርን ከ30 ከበለጠ በ30 እገደፍን እናገኛለን፡፡
~ ነነዊ ፆም + ዓብይ ፆም -30
~ዓብይ ጾም ተውሳኩ 14 ነው
14 +29= 43 ሲሆን ስለዚህ ዘንድሮ በዘመነ ሉቃስ ዓብይ ጾም በየካቲት 13 ይገባል ማለት ነው፡፡
~ደብረ ዘይት፡ ተውሳኩ 11 ነው፡፡
11+29 =40 ይሆናል፡፡ 40 ከ 30 ስለሚበልጥስና በየካቲት ስላለፍን ቀጣዩን በመጋቢት እናገኛለን። ስለዚህ መጋቢት 10 እሁድ ደብረዘይት ይሆናል።
~ሆሣዕና ተውሳኩ 2 ነው፡፡
2+29 =31 ሚያዚያ 1 እሁድ ይሆናል፡፡
~ስቅለት ተውሳኩ 7 ነው።
7+29=36 ሚያዚያ 6 አርብ ይሆናል
~ትንሣኤ ተውሳኩ 9 ነው።
9+29=28 ሚያዚያ 8 እሁድ ይሆናል።
~ርክበ ካህናት ተውሳኩ 3 ነው።
3+29=32 ግንቦት 2 ረቡዕ ይሆናል።
~ዕርገት ተውሳኩ 18 ነው።
18+29=47 ግንቦት 17 ሐሙስ ይሆናል።
~ጰራቅሊጦስ ተውሳኩ 28 ነው።
28+29=57 ከ30 በላይ ስለሆነ ይገደፋል ይኸውም 27 ነው ግንቦት 27 እሁድ ይሆናል።
~ፆመ ሐዋርያት ተውሳኩ 29 ነው።
29+29=58 በ30 ሲገደፍ 28 ይሆናል ማለትም ግንቦት 28 ሰኞ ይሆናል።
~ፆመ ድኅነት ተውሳኩ 1 ነው።
1+29= 30 ግንቦት 30 ረቡዕ ይሆናል ማለት ነው።
ሌሊት = የዓመቱ አበቅቴ + እለት + እፀፆ ከ30 ከበለጠ በ30 እንገድፍለን ቀሪዉን እንይዛለን ።
እፀፆ=መስከረምና ጥቅምት 1
ህዳርና ታህሳስ 2 ወዘተ___

ጨረቃ= ሌሊት + 4 (የጨረቃ ተዉሳክ )
ምሳሌ ፦ 01/01/2015 ዓ.ም ሌሊቱንና ጨረቃዉን አግኝ ?
ሌሊት =የአመቱ አበቅቴ + እለት + እፀፆ
የአመቱ አበቅቴ =9
እለት =1
እፀፆ =1
ሌሊት =9+1+1
ሌሊት=11
ጨረቃ =ሌሊት + 4
ጨረቃ=11+4
ጨረቃ=15

ባሕረ ሐሳብ📜 📚.የ2015 ዓ.ም የአጽዋማትና የበዓላት አቆጣጠር እና አወጣጥ፦✍የአፅዋማትን እና በዓላትን አወጣጥ የምንመለከት ይሆናል፦✍.ዓመተ ፍዳ ማለት ከክርቶስ ልደት በፊት ያለው ሲሆን ...
12/09/2022

ባሕረ ሐሳብ📜

📚.የ2015 ዓ.ም የአጽዋማትና የበዓላት አቆጣጠር እና አወጣጥ፦
✍የአፅዋማትን እና በዓላትን አወጣጥ የምንመለከት ይሆናል፦
✍.ዓመተ ፍዳ ማለት ከክርቶስ ልደት በፊት ያለው ሲሆን ይኸውም 5500 ዘመን ነው።
✍ .ዓመተ ምህረት ማለት ከክርስቶስ ወዲህ ያለው ዘመን ነው ይኸውም 2015 ዘመን ነው።

📚.ዓመተ ዓለም = ዓመተ ምህረት + ዓመተ ኩነኔ = 2015+ 5500 =7515

📖.ወንጌላዊው ማን እንደሆነ ለማወቅ፦
ዓመተ ምህረት + ዓመተ ፋዳ ÷ 4
~7515 ÷ 4 = 1878 ደርሶ ቀሪ 3 ይሆናል።
~1878 ፦ መጠነ ራብዒት ተብላ ትጠራለች፡፡
~ቀሪው 1 ከሆነ ዘመኑ ዘመነ ማቴዎስ
~ቀሪው 2 ከሆነ ዘመኑ ዘመነ ማርቆስ
~ቀሪው 3 ከሆነ ዘመኑ ዘመነ ሉቃስ
~ቀሪው 0 ከሆነ ዘመኑ ዘመነ ዮሐንስ ይሆናል።
✍.ስለዚህ ቀሪው 3 ስለሆነ የዘንድሮው ወንጌላዊ ሉቃስ ሲሆን ዘመኑ ዘመነ ሉቃስ ይባላል።

ጥንተ ዮን(ኦን)

~ጥንተ ዮን ማለት መስከረም አንድ የሚውልበት ቀን ማለት ነው፡፡
ጥንተ ኦን= ዓመተ ዓለም + መጠነ ራብዒት -1 ÷7(ሰባቱ ዕለታት)
= 7515+ 1878 =9393
= 9393 ÷ 7 = 1341 ቀሪ 6
✍.ከዚህ ቀጥሎ ከቀሪው 6 ላይ 1 እንቀንሳለን ለአለፈው መሸኛ ለሚመጣው መቀበያ ተብሎ 1 ይታተታል(ይቀነሳል) ስለዚህ ከ6-1=5 ይሆናል።
✍.ጥንተ ኦን ከእሁድ ይጀምራል፦
ቀሪው 1 ከሆነ ረቡዕ
ቀሪው 2 ከሆነ ሐሙስ
ቀሪው 3 ከሆነ ዓርብ
ቀሪው 4 ከሆነ ቅዳሜ
ቀሪው 5 ከሆነ እሁድ
ቀሪው 6 ከሆነ ሰኞ
ቀሪው 0 ከሆነ ማግሰኞ ይሆናል ማለት ነው። በመሆኑም የዘንድሮ 5 ስለሆነ ጥንተ ዮን(የመስከረም መባቻ)እሁድ ይሆናል።
~ ጥንተ እለት (እሁድ) ይጀምራል ።
መባቻ= ዓመተ አለም + መጠነ ራብዓት + 2/7
ሪው 1 ከሆነ እሁድ
ቀሪው 2 ከሆነ ሰኞ
ቀሪው 3 ከሆነ ማክሰኞ
ቀሪው 4 ከሆነ ረቡዕ
ቀሪው 5 ከሆነ ሐሙስ
ቀሪው 6 ከሆነ ዓርብ
ቀሪው 0 ከሆነ ቅዳሜ ይሆናል ማለት ነው።
~ጥንተ ቀመር (ማክሰኞ) ይጀምራል ።
መባቻ= ዓመተ አለም+መጠነ ራብዓት/7
ሪው 1 ከሆነ ማክሰኞ
ቀሪው 2 ከሆነ ረቡዕ
ቀሪው 3 ከሆነ ሐሙስ
ቀሪው 4 ከሆነ ዓርብ
ቀሪው 5 ከሆነ ቅዳሜ
ቀሪው 6 ከሆነ እሁድ
ቀሪው 0 ከሆነ ሰኞ ይሆናል ማለት ነው።
ወንበር
📚.ወንበር =ዓመተ አለም ÷19 ወይም
ወንበር × ጥንተ አበቅቴ = አበቅቴ
ወንበር × ጥንተ መጥቅዕ =መጥቅዕ
ወንበርን ለማግኘት የአብይ ቀመር የጊዜው መደቡን በእድያው አባዝተን ከዓመተ ዓለሙ ላይ መቀነስ ከዛ በ19 መግደፍ ማለትም፦
~ (7515/19)_1
~7515-7505= 10
ከቀሪው ላይ ላለፈው መሸኛ ለሚመጣው መቀበያ አንድ እናትታለን ከዛ ወንበርን እናገኛለን።
ወንበር =10 - 1= 9 ይሆናል።
አበቅቴ
📚.አበቅቴ ፦ጥንተ አበቅቴን በወንበር አባዝተን በ30 ገድፈን እናገኛለን።
አበቅቴ = ጥንተ አበቅቴ*ወንበር ÷30
11*9=99
99፥30= 3 ደርሶ ቀሪው 9 ሲሆን የዘንድሮ አበቅቴ 9 ይሆናል።
አበቅቴን ለማግኘት ሌላው አማራጭ አበቅቴ እና መጥቅዕ ድምራቸው ከ30 አይበልጡም አያንሱም ስለዚህ አንዱን ካገኘን ከ30 ላይ ቀንሰን ማግኘት ይቻላል።
መጥቅዕ
📚.መጥቅዕ፦ ጥንተ መጥቅዕን በወንበር አባዝተን ለ30 በመግደፍ(በማካፈል) እናገኛለን።
መጥቅዕ =ጥንተ መጥቅዕ*ወንበር ÷30
19×9 = 171
171 ÷ 30= 5 ቀሪው 21 ስለሆነ መጥቅዕ ዘንድሮ 21 ይሆናል።
መጥቅዕን ለማግኘት ሌላው አማራጭ መጥቅዕን ወይ አበቅቴ ካገኘን ከ30 መቀነስ ነው።
“አበቅቴ ወመጥቅ ክሌሆሙ ኢይበዝሁ እም30 ወኢይኅዱ እም 30 ወትረ ይከዉኑ 30 ፤ አበቅቴ ቢበዛ መጥቅ ቢያንስ

05/09/2022

የሰው ልብ መንገዱ ያዘጋጃል፤ እግዚአብሔር ግን አካሄዱን ያቀናለታል። መፅሃፉ ምሳሌ ፲፮፤፱

Address

Gebeze Mariam
Injibara
09

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kibrit Getie posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share