Ethiopian Banking Information -EBI- የኢትዮጵያ የባንክ መረጃ

Ethiopian Banking Information -EBI- የኢትዮጵያ የባንክ መረጃ We provide you the latest and fundamental information about Ethiopian Banking Sector.

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሳይበር ደህንነት ስርዓቱን ይበልጥ ለማጠናከር እና የደንበኞችን ገንዘብ ከዘራፊዎች ለመጠበቅ የሚያስችል ዘመናዊ የ AI ቴክኖሎጂ ማስተዋወቁን አስታውቋል።ይህ የተገለጸ...
17/08/2026

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሳይበር ደህንነት ስርዓቱን ይበልጥ ለማጠናከር እና የደንበኞችን ገንዘብ ከዘራፊዎች ለመጠበቅ የሚያስችል ዘመናዊ የ AI ቴክኖሎጂ ማስተዋወቁን አስታውቋል።
ይህ የተገለጸው የባንኩ የኢንፎርሜሽን ሲስተም ደህንነት ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ስዩም ዳምጠው ሰሞኑን በአዲስ አበባ በተካሄደው 29ኛው የ'Connected Banking Summit' ላይ ባቀረቡት ሪፖርት ነው።

የቴክኖሎጂው ዋና ዋና ጥቅሞች፦

🤖 የግብይት ማጭበርበርን በቅጽበት መለየት፦ ቴክኖሎጂው የደንበኞችን መደበኛ የገንዘብ ዝውውር ባህሪ በማጥናት፣ ያልተለመደ እና አጠራጣሪ እንቅስቃሴ ሲፈጠር በቅጽበት ይለያል። አደጋ (Risk) መኖሩን ሲያረጋግጥም ዝውውሩን ያገዳል ወይንም ተጨማሪ ማረጋገጫ (Verification) ይጠይቃል።

📱 የሞባይል ባንኪንግ ደህንነት ጥበቃ (RASP)፦ በደንበኞች ስልክ ላይ ሊኖሩ የሚችሉ አደገኛ ቫይረሶችን (Malware) እና ያልተፈቀዱ የጠላፊዎች አፕሊኬሽኖችን በመለየት፣ ስጋት ሲፈጠር አጠራጣሪ ዝውውሮችን ወዲያውኑ ያቋርጣል።

🔒 'Zero Trust' (ማንንም አለማመን) መርህ፦ ሲስተሙ የትኛውንም ተጠቃሚም ሆነ መሳሪያ በዘፈቀደ ከማመን ይልቅ፣ በእያንዳንዱ የኔትዎርክ እንቅስቃሴ ላይ ተከታታይ እና ጥብቅ ማረጋገጫዎችን ይጠይቃል።

ከዚህ በተጨማሪም ባንኩ ከሶስተኛ ወገን (Third-party) አቅራቢዎች ጋር በሚኖረው የቴክኖሎጂ ትስስር ላይ ጥብቅ የደህንነት ፍተሻዎችን እና የዳታ ልውውጥ ቁጥጥሮችን ተግባራዊ ማድረጉ ተገልጿል።

የፌደራል አቃቤ ህግ በአማራ ባንክ ውስጥ የውጭ ንግድ ስምምነቶችን ሽፋን በማድረግ ከ137 ሚሊዮን ብር በላይ አጉድለዋል ባላቸው ሰባት ተከሳሾች ላይ ክስ መመስረቱ ተሰማ።  አዲስ ፎርቹን እን...
16/08/2026

የፌደራል አቃቤ ህግ በአማራ ባንክ ውስጥ የውጭ ንግድ ስምምነቶችን ሽፋን በማድረግ ከ137 ሚሊዮን ብር በላይ አጉድለዋል ባላቸው ሰባት ተከሳሾች ላይ ክስ መመስረቱ ተሰማ። አዲስ ፎርቹን እንግሊዘኛው ጋዜጣ ዛሬ እንደዘገበው ከተከሳሾቹ መካከል አምስቱ የቀድሞ የባንኩ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ሲሆኑ፣ የቀረበባቸው ክስም ስልጣንን ያለአግባብ መጠቀም እና ከባድ የሙስና ወንጀል መሆኑ ተገልጿል። ጉዳዩ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አምስተኛ የጸረ-ሙስና ችሎት እየታየ ይገኛል።

በክስ መዝገቡ ላይ ስማቸው ከተጠቀሱት የባንኩ ከፍተኛ ሃላፊዎች መካከል የቀድሞው ጊዜያዊ ዋና ስራ አስፈፃሚ ጫንያለው ደሚሴ፣ የኮርፖሬት ባንኪንግ ዳይሬክተሩ ቢዚያም ሰብስቤ፣ የባንኪንግ ቢዝነስ ዋና ኦፊሰሩ ብዙአየሁ ስዩም፣ የሪሌሽንሺፕ ማናጀሩ ምትኩ ታረቀኝ እና የኢንተርናሽናል ባንኪንግ ዳይሬክተሯ ልለለም ጌታቸው ይገኙበታል። ከእነዚህ የባንኩ ሃላፊዎች በተጨማሪም "ዘመራ ኢንቨስትመንት ግሩፕ (ZIG)" የተሰኘ የግል ኩባንያ እና የድርጅቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዘመድኩን ዘውዴ በዚሁ የክስ መዝገብ ተካተው ፍርድ ቤት ቀርበዋል።

አቃቤ ህግ በክሱ ላይ እንዳብራራው፣ የባንኩ ሃላፊዎች የብድር አሰጣጥ እና የቁጥጥር ስርዓቱን ለአንድ ተበዳሪ (ለዘመራ ኢንቨስትመንት ግሩፕ) በሚያመች መልኩ ደረጃ በደረጃ በማጣመም ባንኩን ለከፍተኛ ኪሳራ ዳርገዋል። ሃላፊዎቹ ይህንን ድርጊት የፈጸሙት ለድርጅቱ ህገ-ወጥ ጥቅም ለማስገኘት እና እራሳቸውንም ለመጥቀም በማሰብ መሆኑን አቃቤ ህግ ይሞግታል። ይህ ክስ ከተመሰረተ ገና አራት ዓመት ብቻ በሆነው የአማራ ባንክ ታሪክ ውስጥ ከተከሰቱት እጅግ ከባድ የመልካም አስተዳደር ጥሰት እና የሙስና ቅሌቶች አንዱ ሆኖ ተመዝግቧል።

157 ሚሊዮን mobile banking (money) አካውንት አለን... ግን አሁንም እናቶቻችን ባንክ ለመድረስ አሁንም እስከ 6 ሰዓት ይጓዛሉ! 🚶‍♀️የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ (NBE) ሰሞኑ...
16/08/2026

157 ሚሊዮን mobile banking (money) አካውንት አለን... ግን አሁንም እናቶቻችን ባንክ ለመድረስ አሁንም እስከ 6 ሰዓት ይጓዛሉ! 🚶‍♀️

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ (NBE) ሰሞኑን ያወጣው አዲስ መረጃ እጅግ አስገራሚ እውነታን ይዞ ወጥቷል።
በአንድ በኩል፤ በሀገራችን 157 ሚሊዮን የሚደርሱ የሞባይል ገንዘብ (Mobile Money) አካውንቶች መከፈታቸውን መረጃው ያሳያል። ነገር ግን እውነታው ሲፈተሽ ከነዚህ ሁሉ አካውንቶች ውስጥ በተጨባጭ ስራ ላይ ያሉት እና የገንዘብ ዝውውር የሚደረግባቸው (Active የሆኑት) ከ15% በታች ብቻ ናቸው! ብዙዎቻችን አካውንቱን እንከፍታለን እንጂ የዕለት ተዕለት ህይወታችን አካል አላደረግነውም።

በሌላ በኩል ደግሞ ይበልጥ ልብ የሚነካ እና አሳሳቢ ክፍተት አለ። እኛ በከተማ ያለን ሰዎች ባለበት ቦታ ሆነን በስልካችን በሰከንዶች ውስጥ ክፍያዎችን ስንፈጽም፣ በገጠር የሚኖሩ እናቶች እና እህቶቻችን መሰረታዊ የባንክ አገልግሎት ለማግኘት ብቻ በአማካይ ለ6 ሰዓታት መንገላታት ግድ ይላቸዋል።

157 ሚሊዮን የዲጂታል አካውንት ባለባት ሀገር፣ አንዲት እናት ገንዘብ ለመቀበል ሙሉ ቀኗን በመንገድ ማሳለፏ ቴክኖሎጂው ገና ብዙ ያልደረሰበት ቦታ እንዳለ ያሳያል።

ይህን ሰፊ ክፍተት ለመቅረፍ ብሔራዊ ባንክ አዲስ የዲጂታል ክፍያ ስትራቴጂ (Digital Payments Strategy 2.0) ይፋ አድርጓል። ከዚህ በኋላ የባንኩ ትኩረት የሚሆነው "አካውንቶችን በቁጥር ማብዛት" ሳይሆን፣ ተደራሽ ያልሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች በተለይም የገጠሩ ማህበረሰብ የዲጂታል ፋይናንሱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ላይ ነው ተብሏል።

🗣️ እስኪ እንወያይ፡
ብዙ ሰው ሞባይል ባንክ አካውንት ከፍቶ የማይጠቀምበት ዋነኛ ምክንያት ምንድነው ትላላችሁ? የኔትወርክ ችግር፣ የእምነት (Trust) ማጣት፣ ወይስ አሁንም ጥሬ ገንዘብ ይበልጥ ስለሚመቸን?

ደግሞስ የገጠሩን ማህበረሰብ የልፋት 6 ሰዓት በእርግጠኝነት ለማስቀረት የትኛው አካል (መንግስት፣ ባንኮች ወይስ ቴሌኮም) ምን ቢሰራ ይሻላል?
ሀሳባችሁን ከታች በኮመንት ያካፍሉን! 👇

የማትጊያ ክፍያ ሲባል ሠራተኛው ስለሠራ ነው እንዲሠራ ነው Bonus የተሠጠው?
15/08/2026

የማትጊያ ክፍያ ሲባል ሠራተኛው ስለሠራ ነው እንዲሠራ ነው Bonus የተሠጠው?

የአማራ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ይህንዓለም አቅናው አቀባበል በፎቶ፡፡በአቀባበል ስነ-ስርዓቱ የአማራ ባንክ  የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት እና ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን ለዋና...
15/08/2026

የአማራ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ይህንዓለም አቅናው አቀባበል በፎቶ፡፡

በአቀባበል ስነ-ስርዓቱ የአማራ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት እና ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን ለዋና ስራ አስፈፃሚውም መልካም የስራ ዘመን ተመኝተዋል፡፡

#አማራባንክ

ዋናውን ዲዛይን አሳዩን ላላቹ
15/08/2026

ዋናውን ዲዛይን አሳዩን ላላቹ

አቶ አብዱልጁሃድ ሹመታቸው በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የፀደቀው ፤ በ9 ወራት ውስጥ የባንኩ ትርፍ በ10 ዕጥፍ፣ ተቀማጩ ደግሞ በሁለት ዕጥፍ ማደጉን ተከትሎ ነው።ባንኩ በሽግግር ወራቱ ባሳየው ...
15/08/2026

አቶ አብዱልጁሃድ ሹመታቸው በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የፀደቀው ፤ በ9 ወራት ውስጥ የባንኩ ትርፍ በ10 ዕጥፍ፣ ተቀማጩ ደግሞ በሁለት ዕጥፍ ማደጉን ተከትሎ ነው።

ባንኩ በሽግግር ወራቱ ባሳየው ከፍተኛ ዕድገት ያልተጣራ ትርፉ 231 ሚሊዮን ብር ደርሷል።

የተቀማጩ መጠን 4.7 ቢሊዮንን ብር ሲደርስ ፤ 425 ሺህ 693 ደምበኞች ማፍራቱንም ከአዲስ ፎርቹን የተገኘው መረጃ ጠቁማል።

Zemen Bank Bonus and Salary Increament 👏👏👏👏👏
15/08/2026

Zemen Bank Bonus and Salary Increament 👏👏👏👏👏

ወጋገን ባንክ የአካባቢያዊ፣ ማህበራዊ እና አስተዳደራዊ (ESG) መርሆችን ያማከለ የዲጂታል ባንኪንግ አገልግሎት በመስጠት ኢንተርናሽናል ሴንተር ፎር ስትራቴጂክ አሊያንስ (ICSA) ባዘጋጀው ...
15/08/2026

ወጋገን ባንክ የአካባቢያዊ፣ ማህበራዊ እና አስተዳደራዊ (ESG) መርሆችን ያማከለ የዲጂታል ባንኪንግ አገልግሎት በመስጠት ኢንተርናሽናል ሴንተር ፎር ስትራቴጂክ አሊያንስ (ICSA) ባዘጋጀው Innovation & Excellence Awards መድረክ ላይ ሸልማት አገኘ፡፡ ይህ ሽልማት የዲጂታል ፉይናንስ መፍትሔዎችን በማስፉፉት እና የፉይናንስ አካታችነትን በማጎልበት ባንኩ ላበረከተው አስተዋፅኦ እውቅና የሰጠ ነው::

ገዳ ባንክ አዲስ የሚያስገነባውን የህንፃ ዲዛይን ይፋ አደረገ፡፡ባንኩ አስገነባዋለሁ ያለው ዋና መስሪያ ቤት ሜክሲኮ አካባቢ በ6 ሺህ 579 ካሬ ሜትር ላይ እንደሚያርፍም ተናግሯል፡፡ገዳ ባንኩ...
14/08/2026

ገዳ ባንክ አዲስ የሚያስገነባውን የህንፃ ዲዛይን ይፋ አደረገ፡፡

ባንኩ አስገነባዋለሁ ያለው ዋና መስሪያ ቤት ሜክሲኮ አካባቢ በ6 ሺህ 579 ካሬ ሜትር ላይ እንደሚያርፍም ተናግሯል፡፡

ገዳ ባንኩ ይፋ ያደረገው የህንፃው ዲዛይን የኪነ-ሕንፃ ጥበብን ከዘመናዊ ቴክኖሎጂ ጋር ያቀናጀ መሆኑን የተናገሩት የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ወልዴ ቡልቶ የዋና መሥሪያ ቤት ግንባታ ለማካሄድ የዲዛይን ውድድር ሲያካሂድ ቆይቷል ብለዋል።

ውድድሩ በዘርፉ በታወቁ ገለልተኛ ዳኞች ጥብቅ ምዘና ሲደረግበት የቆየ መሆኑ የተነገረ ሲሆን መስፈርቱን አሟልተው ለውድድር ከቀረቡ 18 ተወዳዳሪዎች አንድ ድርጅት አሸንፏል ተብሏል።

ወደ ስራ ከገባ ሶስት አመታትን ያስቆጠረው ገዳ ባንክ ከ32 ሺህ በላይ ባለአክሲዮኖች እንዳሉት ያነሳ ሲሆን ጠቅላላ ሀብቴ 12.6 ቢሊየን ብር ማደግ ችሏል ብሏል።

በተጨማሪም እስካሁን ከ110 በላይ ቅርንጫፎችን መክፈቱን የተናገረ ሲሆን በተጠናቀቀው በጀት አመትም ከ1 ቢሊየን ብር በላይ ትርፍ ማግኘቱን ባንኩ አስረድቷል።

Source Sheger FM 102.1

Address

Addis Ababa
611-0011

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Banking Information -EBI- የኢትዮጵያ የባንክ መረጃ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share