Solomon Agizew

Solomon Agizew This is Solomon Agizew's Official page.

07/08/2022

አንዳንዴ ህይወት የማትችለውን
እንድትጋፈጥ ታደርግሃለች ትልቁ ፈተና ግን 👇

👉 ትልቁ ፈተና መሞት አይደለም አለመኖር እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና መፀለይ አይደለም አለማመን እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና ማፍቀር አይደለም አለመፅናት እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና መደመር አይደለም አለማካፈል እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና ማጣት አይደለም ተስፋ መቁረጥ እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና ማግባት አይደለም አለመግባባት እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና መደሰት አይደለም ደስታን አለመቆጣጠር እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና ማሰብ አይደለም የሚያስቡትን አለማጤን እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና ችግር አይደለም ትዕግስት ማጣት እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና ማዘን አይደለም ማማረር እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና ሃይማኖተኛ መሆን አይደለም መንፈሳዊ መሆን እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና ስልጣን አይደለም አጠቃቀሙን አለማወቅ እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና እውቀት አይደለም እያወቁ መሳሳት እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና ስደት አይደለም የተሰደዱለትን አላማ መርሳት እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና ስኬታማ መሆን አይደለም ራዕዩን መርሳት እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና የፀለዩትን ማግኘት አይደለም ያገኙትን ማማረር እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና ዝምተኛ መሆን መቻል አይደለም በዝምታ ውስጥ መረጋጋት ማጣት እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና ቤተክርስትያን ወይም መስጊድ መሄድ አይደለም የሚሄዱበት ምክንያት መዛባት እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና ገንዘብ አይደለም በገንዘቡ የምናደርግበትን ነገር አለማስተዋል እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና ልጅ መውለድ አይደለም ልጅን መቅረፅ እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና መጣላት አይደለም ለበቀል ማቀድ እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና ይቅርታ ማድረግ አይደለም ይቅርታውን ማመን እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና መለያየት አይደለም እንደሚገናኙ አለማሰብ
እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና ፈጣሪን ማሰብ አይደለም ፈጣሪን ማመን እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና መጣላት አይደለም ክፉ ቃል መናገር እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና ተሰሚነትን መጨመር አይደለም ለሚሰሙን መልካም አርአያ መሆን እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና አብሮ ስራ መጀመር አይደለም አብሮ ስራውን መፈፀም እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና አለማቀድ አይደለም ለማቀድ አለመሻት እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና ሞክሮ መበላሸት አይደለም ድጋሚ አለመሞከር እንጂ
👉 ትልቁ ፈተና ጓደኛ ማጣት አይደለም ወዳጅ ማግኘት እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና ማሸነፍ መቻል አይደለም አሸንፎ መፅናት እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና ተመስገን ማለት አይደለም አመስግኖ መርካት እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና መደንገጥ አይደለም ግራ መጋባት እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና መሸነፍ አይደለም ተሸንፎ መቅረት እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና እንደ እዮብ መውደቅ አይደለም እንደ እዮብ መፅናት እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና ከልብ ማልቀስ አይደለም ተሰብሮ መቅረት እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና ሀገርን መውደድ አይደለም ሀገርን ማገልገል እንጂ!
👉 ትልቁ ፈተና ሰው ሆኖ መፈጠር አይደለም ሰው ሆኖ መኖር እንጂ! ✔
•••═• 🌼🍀🌹•••═•

You can Earn $1 in every click!https://instapay.work/?ref=tjMqUxi8
01/12/2021

You can Earn $1 in every click!

https://instapay.work/?ref=tjMqUxi8

Get $5 Instant Cash,Share Your Referral Link and Get $1 for Each Visitors.Withdraw Your Cash to Paypal,Bitcoin,Paytm.

26/11/2021
በቀላሉ የእጅ ስልክዎትን በመጠቀም ተጨማሪ ገንዘብ ማግኘት ይፈልጋሉ?? ከታች ያስቀመጥኩትን ቅደም ተከተል በመጠቀም ይሞክሩት። ጥያቄ ካለዎት ይፃፉልኝ።፨Do you want additional i...
26/11/2021

በቀላሉ የእጅ ስልክዎትን በመጠቀም ተጨማሪ ገንዘብ ማግኘት ይፈልጋሉ?? ከታች ያስቀመጥኩትን ቅደም ተከተል በመጠቀም ይሞክሩት። ጥያቄ ካለዎት ይፃፉልኝ።

Do you want additional income?? Make money easily on your phone, mine bitcoin and earn $$$. Let me show you how:-

👉1st. Download the app on your phone, install, register and confirm your identity. Click on the link below to download.
👉 https://www.btcs.love/invite/2dz5e

👉 Invitation Code: 2dz5e

👉2nd. Login in and click on mining tab then click on mine button.

👉3rd. Use the following Gift Card codes to increase your mining speed.

Gift card:30K hashrate each
3b82htq 👈 Copy Code
3b82htq 👈 Copy Code
3bckbbv 👈 Copy Code
3beuqky 👈 Copy Code
3bh54uy 👈 Copy Code

How to use Gift card and increase your mining power by 30K/s press join Gift card, fill any code and then confirm steps by step photos tutorial below

👍If you have any questions let me know on comment box. Thank You!!

27/05/2021
ቀብር : ደብረ ታቦር ከተማየብርጋዴር ጄኔራል ኃይሌ መለስ አስከሬን ስርዓተ ቀብር በደቡብ ጎንደር ዞን ደብረ ታቦር ከተማ ደብረልዑላን መድኀኒዓለም ቤተ ክርስቲያን ተፈፀመ፡፡ብርጋዴር ጄኔራል ...
16/05/2021

ቀብር : ደብረ ታቦር ከተማ
የብርጋዴር ጄኔራል ኃይሌ መለስ አስከሬን ስርዓተ ቀብር በደቡብ ጎንደር ዞን ደብረ ታቦር ከተማ ደብረልዑላን መድኀኒዓለም ቤተ ክርስቲያን ተፈፀመ፡፡
ብርጋዴር ጄኔራል ኃይሌ መለስ በ1933 ዓ/ም እንደተወለዱ የሚነገርላቸው ሲሆን ወደ ውትድርናው ዓለም የተቀላቀሉት ገና በልጅነት ዕድሜያቸው ነበር።

የቆሎ ተማሪ ይመስል ነፀነትን ከጠላቶችህ አትለምን፣ ነፃነት በደም እንጂ በልመና አይገኝም!!።

በማለት በጠላቶቹ ፊት በድፈረት የተናገረ ቆራጥ ጀግና ነበረ፡፡
ብርጋዴር ጄኔራል ኃይሌ መለስ በዚያድ ባሬ የተመራውን የሶማሊያ ጦር ኢትዮጵያን በወረረበት ዘመን የኢትዮጵያን ጦር የመሩና ድልንም የተቀዳጁ የነፃነት ፋና ወጊ ታላቅ አባት ነበሩ።
‘እጄን ለጠላት አንከርፍፌ እንድሰጥ ትከሻየ ላይ የጫንኩት ማዕረግ፣ከአባቶቼ የወረስኩት ወኔ፣ለወገኔ እና ለእናት ሀገሬ የገባሁት ቃል ኪዳን አይፈቅድልኝም” በማለት በኩራትና በድፍረት የተናገሩ የካራማራው መብረቅ እንደነበሩና በ1983 ዓ/ም እናት ሀገሬን ለወያኔ ትቼ አልሄድም በማለት ፊቱን ወደ ጫካ በማዞር የሰሜኑ ግንባር የጦር ጄኔራሎች ወደ መሃል ሀገር ሲሸሹ እርሱ ግን ተፈጥሮ በቸረው የደቡብ ጎንደር ዞን ጫካ በመግባት ወያኔን ከጀርባ ሆኖ ያርበተበተ ጀግና ሲሆን ከ1983 እስከ 1989 ዓ/ም ድረስ በሰሜን ተራሮ እና ሸለቆዎች በመመሸግ በስሙ ብቻ ወያኔዎችን ሢያሸብር መቆየቱ የታሪክ ድርሳናት ይመሰክራሉ፡፡
በመጨረሻም የብርጋዴር ጀኔራል ኃይሌ መለስ የለቅሶ ስነ-ስርዓት በአማረና በደመቀ ሁኜታ በአብክመ ፖሊስ ማርሽ ባንድ.፣ በአማራ ልዩ ኃይልና በደቡብ ጎንደር ዞን መለዮ ለባሽ የፖሊስ አባላት በክብር ታጅቦ ውሎ የቀብር ስርአቱ በደብረ ታቦር ከተማ ደብረልዑላን መድኀኒዓለም ቤተ ክርስቲያን ከቀኑ በ7፡00 ስዓት ተከናውኗል፡፡
© ጌጡ ተመስገን

ውድ የእስልምና ዕምነት ተከታይ ለሆናችሁ ሁሉ እንኳን ለ1442ኛው ኢድ አል ፈጥር በሰላም አደረሳችሁ!! ፨መልካም በዓል!!
13/05/2021

ውድ የእስልምና ዕምነት ተከታይ ለሆናችሁ ሁሉ እንኳን ለ1442ኛው ኢድ አል ፈጥር በሰላም አደረሳችሁ!!

መልካም በዓል!!

ዩኒቨርሲቲውን እንውቀስ ወይስ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ያሉትን መምህራን ፣ አመራሮችን ፣ ተማሪዎችን???መቼም ይሄን ስህተት ልክ እንደ ተራ ስህተት አድርገን ካለፍነው ትውልድ መግደያ ፋብሪካውን ...
10/05/2021

ዩኒቨርሲቲውን እንውቀስ ወይስ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ያሉትን መምህራን ፣ አመራሮችን ፣ ተማሪዎችን???

መቼም ይሄን ስህተት ልክ እንደ ተራ ስህተት አድርገን ካለፍነው ትውልድ መግደያ ፋብሪካውን እያስፋፋነው እንደሆነ ይቆጠራል።

እስኪ እነዚህን ሁለት ኢትዮጵያዊያንን ለሀገራቸው ባበረከቱትን አስተዋፅኦ ልክ እንመዝናቸውና ሀሳባችንን እናጋራ!!"ሌ/ጀ ጃጋማ ኬሎ"  እና  "ጀኔራል? ዋቆ ጉቱ"
20/04/2021

እስኪ እነዚህን ሁለት ኢትዮጵያዊያንን ለሀገራቸው ባበረከቱትን አስተዋፅኦ ልክ እንመዝናቸውና ሀሳባችንን እናጋራ!!

"ሌ/ጀ ጃጋማ ኬሎ" እና "ጀኔራል? ዋቆ ጉቱ"

18/04/2021

ዛሬ የኢፌዴሪ መከላከያ ሚንስቴር ምን ብሎ መግለጫ ቢያወጣ ጥሩ ነው??

"ቤተ ክርስትያንና ቤት ማቃጠል፣ ማውደም የተከለከለ ነው።" !!

ኢትዮጵያ ለህዝቧ ተጨንቃ ሰላም ሚኒስቴርን አቋቋመች አሉ፣ህዝብ ሰላሙን አጥቷልሰራተኞቹ የክት ልብስ ያሰፋሉ፣ደግሞ ይባስ ብለው ምነውሰላሙን ያጣውን ህዝብ ሰላም ነህ ባይሉ!!
17/04/2021

ኢትዮጵያ ለህዝቧ ተጨንቃ
ሰላም ሚኒስቴርን አቋቋመች አሉ፣

ህዝብ ሰላሙን አጥቷል
ሰራተኞቹ የክት ልብስ ያሰፋሉ፣

ደግሞ ይባስ ብለው ምነው
ሰላሙን ያጣውን ህዝብ ሰላም ነህ ባይሉ!!

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ 3ኛ ዓመት በዓለ ሲመት በኦሮሚያ ደረጃ እየተከበረ ነው።በኦሮሚያ የንፁሀን ደም እንደ ጎርፍ ይወርዳ ፣ የእናቶች እንባ አልቆም ብሏል። የኦሮሚያ ክልል የሀዘን...
02/04/2021

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ 3ኛ ዓመት በዓለ ሲመት በኦሮሚያ ደረጃ እየተከበረ ነው።

በኦሮሚያ የንፁሀን ደም እንደ ጎርፍ ይወርዳ ፣ የእናቶች እንባ አልቆም ብሏል። የኦሮሚያ ክልል የሀዘን ቀን ያውጃል ብሎ ህዝብ ሲጠብቅ ባለስልጣኑ በሙሉ በሸራተን ሆቴል ተሰብስቦ በቅንጡ ምግብና መጠጥ ለደስታችን "Cheer's!" ይባባላሉ!!

ያሳፍራል!!

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የማጣርያ ጉዞውን በአሰልጣኝ አብርሃም መብራቱ (2 ጨዋታ) መሪነት ጀምሮ በአሰልጣኝ ውበቱ አባተ (4 ጨዋታ) መሪነት ወደ አፍሪካ ዋንጫ በማለፍ አጠናቋል።ክብር ለአሰ...
30/03/2021

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የማጣርያ ጉዞውን በአሰልጣኝ አብርሃም መብራቱ (2 ጨዋታ) መሪነት ጀምሮ በአሰልጣኝ ውበቱ አባተ (4 ጨዋታ) መሪነት ወደ አፍሪካ ዋንጫ በማለፍ አጠናቋል።
ክብር ለአሰልጣኞቻችን እናመሰግናለን።

ኢትዮጵያዊያን እንኳን ደስ አላችሁ ፣ እንኳንም ደስ አለን!!
30/03/2021

ኢትዮጵያዊያን እንኳን ደስ አላችሁ ፣ እንኳንም ደስ አለን!!

አንዳንዴ ኢትዮጵያ ደራርቱ ቱሉን ትመስለኛለች!!***********************************************፨ አያት አደባባይ "ደራርቱ ቱሉ አደባባይ" ተብሎ ተሰየመ።፨ የ202...
28/03/2021

አንዳንዴ ኢትዮጵያ ደራርቱ ቱሉን ትመስለኛለች!!
***********************************************
፨ አያት አደባባይ "ደራርቱ ቱሉ አደባባይ" ተብሎ ተሰየመ።
፨ የ2021 አዲስ ሞዴል ሌክሰስ መኪና ተሸለመች።
፨ ፌደራል ማረሚያ ፩ኛ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰጠ የክብር ኒሻን ሽልማት ሸለማት።
፨ አዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር ሁለት ሚሊየን ብር ሰጣት።
፨ ኦሮሚያ ክልል አምስት ሚሊየን ሸልሟታል።
፨ ሱሉልታ ያለ የስፓርት አካዳሚ በስሟ ተሰይሞላታል።
፨ 350 ግራም የክብር ኒሻን በኮሚቴው አስተባባሪነት በባለሀብቶች ተሸለመች።
፧ ለዚች ጀግና ኢትዮጵያዊት ይህም የሚያንስባት ቢሆንም እንዲህ ለኢትዮጵያ ውለታ የዋሉ ሰዎችን በህይወት እያሉ ምስጋና ማቅረብ ይገባናል።

17/03/2021

በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውስጥ የጉሙዝ ብሄረሰብ አባላት የሆኑት በማመፅ ፣ ወደ ጫካ በመግባት ፣ ከኢትዮጵያ ጠላቶች የትጥቅ ፣ የስንቅና የስልጠና ድጋፍ በማግኘት በክልሉ የተለያየ ቦታ ላይ በሚኖሩ የአማራና ሌሎች ብሄሮችን በአሰቃቂ ሁኔታ ሲጨፈጭፍ ፣ ቤት ሲያቃጥል ፣ ሲያፈናቅል ከሁለት አመት በላይ መቆየቱ ይታወቃል።

ህዝብም መንግሥት በሀገር መኖሩን እስኪጠራጠር ድረስ ገዳዮችን በዝምታ ሲመለከት ይባስ ብሎ የመንግስት አካላት ድጋፍ ሲደረግላቸው መቆየቱን ይፋ ሆኗል።

እነኚህ ዘግናኝ ጭካኔ የተሞላበት ግድያ እንዳሻቸው ሲፈፅሙ የነበሩ ታጣቂዎች በመንግስት የፀጥታ አካላት ተይዘው ለፍርድ እንዲቀርቡ አለያም ባሉበት እንዲደመሰሱ ይደረጋል ብለን ስንጠብቅ ምን ቢሆን ጥሩ ነው?

እጃቸውን በሰላማዊ መንገድ ስለሰጡ አፉ ብለናቸው በሆነ አዳራሽ ሰብስበን ተሀድሶ ሰጥተናቸዋለን ....... ከዛ ወደ ቤታቸው ገብተው በሰላም ይኖራሉ እያለን ነው መንግሥት።

Mission Accomplished!!

በዓመት አንድ ቀን "March 8" የሴቶችን ቀን ከማክበር ይልቅ ዘወትር በየዕለቱ ሴቶችን እናክብር!!
08/03/2021

በዓመት አንድ ቀን "March 8" የሴቶችን ቀን ከማክበር ይልቅ ዘወትር በየዕለቱ ሴቶችን እናክብር!!

Address

Addis Ababa
121

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Solomon Agizew posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The University

Send a message to Solomon Agizew:

Share