26/08/2026
የቴክኒክና ሙያ በ5ዓመታት የተመዘገቡ ለውጦች
የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ባለፉት አምስት ዓመታት ያስመዘገባቸው ለውጦች
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከተቋቋመ አምስት ዓመታትን አስቆጥሯል፡፡
በዚህ ጊዜ ውስጥ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የነበሩ ማነቆዎችን ለመፍታት አጠቃላይ የህግና የማዕቀፍ ለውጦችን አድርጓል፡፡
የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ተሻለ በሬቻ እንዳብራሩት፤ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ከዚህ በፊት ሲመራበት የነበረው የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በአዲስ መልክ ተከለሶ ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡
በተጨማሪም አዲስ የቴክኒክና ሙያ ስትራቴጂ እንዲሁም የቴክኒክና ሙያ፣ ከፍተኛ ትምህርት፣ የምርምር እና የኢንዱስትሪ ትስስር አዋጅ መሻሻላቸው በዚህ የአምስት ዓመት ጉዞ ውስጥ የሚጠቀሱ ዋና ዋና ማሻሻያዎች ናቸው፡፡
ይህንን የፖሊሲ ክለሳ ተከትሎ አዲስ ሀገራዊ የብቃት ማዕቀፍ የተዘጋጀ ሲሆን ከዚህ ቀደም ተቋማቱ እስከ ደረጃ 5 ብቻ ያሰለጥኑ የነበረውን አሰራር በመቀየር አሁን እስከ ደረጃ 8 (ፒ.ኤች.ዲ) ድረስ ማሰልጠን እንዲችሉ ወደ ትግበራ ተገብቷል፡፡
እነዚህ ለውጦች የተደረጉት የዘርፉንና የኢንዱስትሪውን ፍላጎት በማጣጣም ነው፡፡ የአዲሱ ቴክኒክና ሙያ እሳቤ አሰልጥኖ ሰርተፍኬት ከመስጠት ባለፈ ክህሎትን፣ ዕውቀትን የሚያስጨብጥ እና ጥሩ አመለካከትን በዜጎች ላይ የሚቀርጽ እንዲሆን ታስቦ የተሰራበት ነው፡፡
ከዚህ ቀደም ሁሉም የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ተመሳሳይ ስልጠናዎች የሚሰጡበት አሰራር ቀርቶ አሁን የገበያውን ፍላጎትና የአካባቢን ጸጋ መሰረት ያደረገ ስልጠና እንዲሰጡ ተቋማቱ ዘመኑ በሚዋጀው ሁኔታ እንዲደራጁ ተደርገዋል፡፡
ከዚህም ባሻገር ተቋማት ማሰልጠን ብቻ ሳይሆን አምራችና አገልግሎት የሚሰጡ ኢንተርፕሩኒያል መሆን እንዳለባቸው በማድረግ ስልጠናው ይበልጥ ተግባር ተኮር ለማድረግ ተችሏል፡፡
በጠቅላላው ከዛሬ አምስት ዓመት በፊት ከነበረው ሁኔታ ጋር ሲነጻጸር የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ተልዕኮ ግልጽነት የተፈጠረበት እና በብዛት ከማሰልጠን ባለፈ ጥራትንና ተወዳዳሪነትን ማዕከል ያደረገ ሥራ የሚከናወንበት ደረጃ ላይ መድረሱ ተገልጿል፡፡
ነሀሴ 20/2018 ዓ.ም፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
Official Website: mols.gov.et
Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE
Telegram: https://t.me/FDRE_MoLSofficial
TikTok: tiktok.com/
Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር
WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYI