ካምባ ቴክንክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ኮሌጅ 2006 ዓ.ም

  • Home
  • Ethiopia
  • Arba Minch'
  • ካምባ ቴክንክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ኮሌጅ 2006 ዓ.ም

ካምባ ቴክንክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ኮሌጅ 2006  ዓ.ም ካምባ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ

📢  ፣  #ተማሪዎችና  ! 🚀ይህንን ክረምት በከንቱ አያሳልፉ! ካምባ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በፈለጉት የሙያ መስክ  #አሰልጥኖ ለተሻለ የሥራ ዕድልና ለተግባራዊ ስኬት ሊያበቃችሁ ዝግጅቱን አጠናቆ...
10/08/2026

📢 ፣ #ተማሪዎችና ! 🚀

ይህንን ክረምት በከንቱ አያሳልፉ!
ካምባ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በፈለጉት የሙያ መስክ #አሰልጥኖ ለተሻለ የሥራ ዕድልና ለተግባራዊ ስኬት ሊያበቃችሁ ዝግጅቱን አጠናቆ ይጠብቃችኋል!

🌟 በምን ዓይነት የሙያ መስክ #ብቁ መሆን ይፈልጋሉ?

💻 (Computer Skills):
#ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች (ልዩ የክረምት ማጠናከሪያ)
ቤት ባለሙያዎች (በልዩ ሁኔታ ለብቻው የተዘጋጀ)
🏗️ (Building Construction)
🖥️ ስልጠናዎች (Software & Design)
🎍 (Bamboo Crafts & Products)
🔨 (Metalwork & Woodwork)
👗 (Fashion Design)
🔧 / (Automotive & Garage Services)
🐄 ሀብት ልማት (Animal Husbandry … እና ሌሎች በርካታ መስኮች!

💡 ?
እርስዎ ፍላጎትዎትን ብቻ ይወቁ—
እኛ በሙሉ ብቃትና በምርጥ አሰልጣኞች ታግዘን ወደ ስኬት እናሸጋግርዎታለን!

📌 የምዝገባ መረጃ
የምዝገባ ቦታ: ካምባ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
ዒላማ ክፍሎች: ተማሪዎች፣ የሥራ ፈጣሪዎች እና እራሳቸውን ማሳደግ የሚፈልጉ የትኛውም የኅብረተሰብ ክፍሎች
🎯 !
አሁኑኑ ይመዝገቡ!

23/07/2026
‎‎በካምባ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስካሄድ የነበረው የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በላቀ ስኬት እና በሰላም መጠናቀቁ ተገለጸ።‎==========================‎  ሐም...
23/07/2026

‎‎በካምባ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስካሄድ የነበረው የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በላቀ ስኬት እና በሰላም መጠናቀቁ ተገለጸ።
‎==========================
‎ ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም
‎ከካምባ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን

‎በካምባ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሲሰጥ የነበረው የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ያለምንም የቴክኒክም ሆነ የፀጥታ መሰናክል፣ በሙሉ ሰላም እና በፍፁም ስነ-ስርዓት መጠናቀቁን የኮሌጁ ዲን ኢ/ር ግዳጀ ግምቴ ገለጹ።
‎ዲኑ እንደገለጹት፣ የተጣለባቸውን ሀገራዊ ኃላፊነት በስኬት ማሳካት የተቻለው የሁሉም ባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ጥረት; ትብብር እና የባለቤትነት መንፈስ በመታከሉ ሲሆን፣ ለዚህም አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት በሙሉ የላቀ የምስጋና መልዕክት አስተላፍረዋል።

‎ኢ/ር ግዳጀ ግምቴ በመልዕክታቸው፣ የፈተናውን ፍትሃዊነት በማረጋገጥ የስነ-ምግባር ደንቦችን በትግስት እና በኃላፊነት ላስከበሩት ሱፐርቫይዘሮችና ፈተና አስፈታኞች የላቀ ምስጋና አቅርበዋል። አያይዘውም፣ የዲጂታል ፈተናው የቴክኖሎጂና የመሰረተ-ልማት አቅርቦት ሳይስተጓጎል በቅልጥፍና እና በሰዓት ዝግጁነት እንዲካሄድ ላደረጉት የአይሲቲ (ICT) ባለሙያዎችና አሲስታንቶች የማይሰለች የቴክኒክ ድጋፍ አድናቆታቸውን ገልጸዋል።

‎በተጨማሪም፣ በግቢውና በአካባቢው ሙሉ ሰላምና ደህንነት እንዲሰፍን በማድረግ፣ ተፈታኞች በተረጋጋ መንፈስ ፈተናቸውን እንዲወስዱ ላስገኙት አስተማማኝ የጥበቃ አገልግሎት ለፀጥታ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ተፈታኝ ተማሪዎች ላሳዩት አርአያነት ያለው ስነ-ስርዓት እንዲሁም የኮሌጁ ማህበረሰብ እና ሰራተኞች ላደረጉት ሞቅ ያለ እንግዳ ተቀባይነት ያላቸውን አክብሮት ገልጸዋል።

‎በመጨረሻም ዲኑ፣ ሀገራዊ ጥሪን ተቀብለው በየተሰማሩበት ሴክተር ላሳዩት የላቀ ኃላፊነትና ተጋድሎ ምስጋናቸውን እያቀረቡ፣ ለተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ መልካም ውጤትና ብሩህ ተስፋ ተመኝተዋል። ካምባ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ወደፊትም መሰል ሀገራዊ እና ተቋማዊ ኃላፊነቶችን በስኬት ለመወጣት ሁልጊዜም ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።
‎ ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም
‎“ጥራት ያለው ስልጠና ለተግባራዊ እውቀት!
‎የካምባ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ የኦንላይን ፈተና በካምባ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በስኬት እየተሰጠ ይገኛል!ካምባ፣ ሐምሌ 3/2018 ዓ.ም ካምባ ፖሊ ቴ/ኮበጋሞ ዞን ካምባ ከተማ አስተዳደር የ12ኛ ክፍል የተ...
10/07/2026

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ የኦንላይን ፈተና በካምባ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በስኬት እየተሰጠ ይገኛል!
ካምባ፣ ሐምሌ 3/2018 ዓ.ም ካምባ ፖሊ ቴ/ኮ
በጋሞ ዞን ካምባ ከተማ አስተዳደር የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ (Natural Science) ተማሪዎች በካምባ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የተሰጠውን የበይነ መረብ (Online) ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና በሰላምና በታላቅ ስኬት አጠናቀዋል!
የፈተና ጣቢያው ኃላፊ አቶ አበጀ አስራት እንደገለጹት፣ የበይነ መረብ የፈተና ሥርዓት ፍጹም ግልጽነትንና ፍትሃዊነትን በማረጋገጥ ተማሪዎች በራሳቸው አቅምና ችሎታ እውነተኛ ዕውቀታቸውን እንዲያሳዩ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። ተማሪዎች በከተማው በሚገኘው በዚሁ የፖሊቴክኒክ ኮሌጅ መፈተናቸው ለወላጆች አላስፈላጊ የጉዞና የመኖሪያ ወጪን ያስቀረ ከመሆኑም በላይ፣ ተማሪዎች ሳይንቀሳቀሱ በተረጋጋ መንፈስ ሙሉ ትኩረታቸውን ፈተና ላይ እንዲያደርጉ ትልቅ ሥነ-ልቦናዊ እፎይታ ሰጥቷቸዋል።
በተፈጥሮ ሳይንስ ዘርፍ 264 ተማሪዎች (122 ወንድ እና 142 ሴት) በ3 ዙሮች የተሰጠውን ፈተና በሰላም ያጠናቀቁ ሲሆን፣ በመጀመሪያው ዙር ያጋጠመው የካፓሲተር (Capacitor) ብልሽትም በቴክኒክ ባለሙያዎች ፈጣን ርብርብ ወዲያውኑ ተቀርፎ ሂደቱ ያለምንም እንከን እንዲጠናቀቅ ተደርጓል።
የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና በስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ፣ ቀጣይ 228 የማህበራዊ ሳይንስ (Social Science) መደበኛና የግል ተፈታኞች ከሐምሌ 6 እስከ 16 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ከ4ኛ እስከ 6ኛ ዙር ፈተናቸውን በኮሌጁ የሚወስዱ ይሆናል። ተማሪዎችና ወላጆች አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ በተያዘው መርሐ ግብር መሠረት እንዲገኙ ጥሪ ቀርቧል።
ለመላው ፈተናቸውን ላጠናቀቁ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች እንዲሁም ወደ ፈተና ለሚገቡ የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎቻችን በሙሉ ኮሌጃችን የተመኘውን ውጤትና ደማቅ ስኬት እንዲያስመዘግቡ ልባዊ መልካም ምኞቱን ይገልጻል!
#ካምባፖሊቴክኒክኮሌጅ #12ኛክፍልፈተና #የበይነመረብፈተና #ትምህርትበጥራት #የተፈጥሮሳይንስ #የማህበራዊሳይንስ #መልካምምኞት

30/06/2026
🌟 " #በቴክኖሎጂ  #እንቅደም፣  !" 🌟ሰኔ 16/2018 ዓ.ም (ካምባ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ)በጋሞ ዞን ሥራና ክህሎት መምሪያ እና የአርባ ምንጭ ፖሊ ቴክኒክ ሳተላይት ኢንስቲትዩት በክላስተር ...
23/06/2026

🌟 " #በቴክኖሎጂ #እንቅደም፣ !" 🌟

ሰኔ 16/2018 ዓ.ም (ካምባ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ)

በጋሞ ዞን ሥራና ክህሎት መምሪያ እና የአርባ ምንጭ ፖሊ ቴክኒክ ሳተላይት ኢንስቲትዩት በክላስተር አስተባባሪነት ያዘጋጁት ክላስተራዊ የቴክኖሎጂና የተግባቦት ጥናትና ምርምር ውድድርና ኤግዚቢሽን ተጠናቀቀ፡፡

ለኮሌጃችን ማህበረሰብ በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ!
በአርባምንጭ ክላስተር በተካሄደው የ2018 ዓ.ም የቴክኖሎጂ እና ተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድር ኮሌጃችን በክላስተሩ ካሉ ተቋማት ሁሉ #3ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቋል።

እንድሁም በተግባራዊ ጥናትና ምርምር ዘርፍ ኮሌጃችንን በላቀ ብቃት ወክለው የተወዳደሩት #ኢ/ር #ሙሉዓለም #ቦጋሌ በክላስተሩ #1ኛ ደረጃን በመያዝ አሸናፊ በመሆናቸው፣ መላውን የአርባምንጭ ክላስተር ወክለው በክልል ደረጃ ለሚካሄደው ውድድር ተመርጠዋል! 🥇👏

የደቡብ ኢትዮጵያ ሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ኃላፊ የሆኑት ባስተላለፉት ወሳኝ መልዕክት፤ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና (TVET) ሁለት ዋና ዋና ስትራቴጂካዊ ዓላማዎች እንዳሉት ገልጸዋል፡

1️⃣ ብቁ፣ በስነ-ምግባር የታነጸና በክህሎት የዳበረ የሰው ኃይል ለኢንዱስትሪው ማቅረብ፤
2️⃣ የማህበረሰውን ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎችን ሰርቶ ማሸጋገርና ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እቅዶችን ማሳካት።

አክለውም፣ ኮሌጆች በቀጣዩ የ2019 በጀት ዓመት የተግባር ስልጠናን (Practical Training) ከቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራዎች ጋር በማጣመር፣ የሀገር ውስጥ ምርታማነትንና የወጣቶችን የስራ እድል ፈጠራ ማፋጠን እንዳለባቸው አሳስበዋል።

"ዓለም በቴክኖሎጂ ውድድር ውስጥ ናት፤ እኛም በዚህ ውድድር ውስጥ በብቃት መሳተፍ አለብን፤ ካመለጠን የፍትሃዊነት ጥያቄ ማቅረብ የማይቻል፣ የምናቀርብበት አካል የሌለ በመሆኑ ከዘመኑ ቴክኖሎጂ ጋር ለመሄድ ሁሉም መረባረብ አለበት" ሲሉ ያሳሰቡት አቶ በዛብህ፣ የሚፈጠሩ ቴክኖሎጂዎች ለሕዝብ ተጠቃሚነት መዋላቸውን ማረጋገጥ ዋና ግብ መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል።

የአርባ ምንጭ ፖሊ ቴክኒክ ሳተላይት ኢንስቲትዩት ዲንና የክላስተሩ አስተባባሪ በበኩላቸው፣ ተቋሙ ከተግባራዊ ሥልጠና ጎን ለጎን ለችግር ፈቺ ጥናትና ምርምር እንዲሁም ለቴክኖሎጂ ሽግግር ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑን ገልጸዋል። እንደ አቶ በዛብህ ገለጻ፣ ይህ የክላስተር ውድድርና ኤግዚቢሽን የሰልጣኞችንና የአሰልጣኞችን የፈጠራ አቅም በተግባር ለመመዘን እንዲሁም ጥሩ ተሞክሮዎችን ለመለዋወጥ ጠቃሚ ዕድል ፈጥሯል።

በዚህ ኤግዚቢሽኑ ላይ 20 የፈጠራ ሥራዎች ለውድድር የቀረቡ ሲሆን፣ በርካታ አዳዲስ የቴክኖሎጂ ፈጠራዎችና ተግባራዊ የጥናትና ምርምር ውጤቶችም ለዕይታ ቀርበዋል።

እነዚህ የፈጠራ ስራዎች በዳኞች ተገምግመው የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተሳታፊዎች የእውቅናና የሽልማት ፕሮግራም እንደሚካሄድ የተገለጸ ሲሆን፣ እንዲህ ያሉ የፈጠራ ሥራዎችንና የቴክኖሎጂ ሽግግርን ማበረታታት የዲጂታል ኢትዮጵያን ራዕይ እውን ለማድረግ ጉልህ ሚና እንዳለውም ተጠቁሟል።

በመጨረሻም በአሰልጣኝ፣ በሰልጣኝ እና በኢንተርፕራይዝ ዘርፎች በተካሄደው ክላስተራዊ የቴክኖሎጂና የተግባራዊ ጥናት ውድድርና ኤግዚቢሽን አሸናፊ ለሆኑ ተወዳዳሪዎችና ተቋማት የእውቅና ምስክር ወረቀት እና የገንዘብ ማበረታቻ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

23/06/2026

Address

Arba Minch'

Telephone

+251913581237

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ካምባ ቴክንክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ኮሌጅ 2006 ዓ.ም posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share