ታሪካችንን እንወቅ islamic channel

ታሪካችንን እንወቅ islamic channel Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ታሪካችንን እንወቅ islamic channel, College & University, Bahir Dar.

ዓረፋ ዙልሒጃ 9‼️▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬✍የአረፋ እለት አላህ ዲናችንን ያሟላበትና ፀጋውንም የተሟላ ያደረገበት እለት ነው።✅ያቺ እለት አላህ ሱብሃነሁ ወተዓላﺍﻟﻴَﻮﻡَ ﺃَﻛﻤَﻠﺖُ ﻟَﻜُ...
07/07/2022

ዓረፋ ዙልሒጃ 9‼️
▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬
✍የአረፋ እለት አላህ ዲናችንን ያሟላበትና ፀጋውንም የተሟላ ያደረገበት እለት ነው።

✅ያቺ እለት አላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ
ﺍﻟﻴَﻮﻡَ ﺃَﻛﻤَﻠﺖُ ﻟَﻜُﻢ ﺩﻳﻨَﻜُﻢ ﻭَﺃَﺗﻤَﻤﺖُ ﻋَﻠَﻴﻜُﻢ ﻧِﻌﻤَﺘﻲ ﻭَﺭَﺿﻴﺖُ ﻟَﻜُﻢُ ﺍﻹِﺳﻼﻡَ ﺩﻳﻨًﺎ
«ዛሬ ሃይማኖታችሁን ሞላሁላችሁ፣ ፀጋዬንም በናንተ ላይ የተሟላ አደረግኩኝ፣ ኢስላምንም በሃይማኖትነት ወደድኩላችሁ»። በማለት የገለፀበት እለት ናት።

የአላህ መልእክተኛም (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዎል:-

"ﺻﻴﺎﻡُ ﻳﻮﻡِ ﻋﺮﻓﺔَ ، ﺃَﺣﺘﺴﺐُ ﻋﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪِ ﺃﻥ ﻳُﻜﻔِّﺮَ ﺍﻟﺴﻨﺔَ ﺍﻟﺘﻲ ﻗﺒﻠَﻪ، ﻭﺍﻟﺴﻨﺔَ ﺍﻟﺘﻲ ﺑﻌﺪﻩ"
«የዐረፋ እለት ፆም ከዚህ አመት ቀድሞ ያለውንና የቀጣዩን ኣመት እንደሚያስምርልን ከአላህ ኣስባለሁ»።
📒📙📕ሙስሊም ዘግበውታል

በተጨማሪም የአላህ መልእክተኛ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዎል:-
"ﺧﻴﺮُ ﺍﻟﺪﻋﺎﺀِ ﺩﻋﺎﺀُ ﻳﻮﻡِ ﻋﺮﻓَﺔَ ...."
"ከዱዓኦች በላጩ የዐረፋ እለት ዱዓእ ነው"።

ማሳሰቢያ:-
--------------
"የዐረፋ ቀን" ማለት ከዒድ በፊት ያለው ቀን ወይም ነገ ጁሙዓ ነው ሁላችንም የነገውን ቀን እንፁም ለማለት እወዳለሁ።
መልክቱ እናንተ ጋር እንዳይቀር አስተላልፉ።

07/07/2022


ኢማሙ አህመድ አልጋዚ ክፍል 3
━━━━━━━━━━━━━
አያሉ ቢጠሩት “ያ አህመድ ግራኙ”
እሱ እንደው ቀኝ ነው የቀኞችም አውራ
አፄን አሳፍሮ ታሪክ የቀየረ እንደ ጧፍ የበራ

ፋኑኤል የተሰኘ ክርስቲያን የጦር መሪ ከደዋሮ አቅጣጫ ወደ ሁበት ከተማ ሠራዊቱን ይዞ ዘመተ። ወታደሮቹ ሙስሊሙን አጠቁ። ሴት ወንዶችን ያለ ርህራሄ ገደሉ። ሀብት ንብረት ዘረፉ። "የሚቋቋመን ማን አለ?! ጀግና ነኝ የሚል ሙስሊም ይውጣ" በሚል ስሜት ሙስሊም ሕጻናትንና ሴቶችን ማርከው ይዘው ሄዱ። በአቅራቢያው ለነበረው ኢማም አሕመድ ወሬው ደረሰ። የራሱን ሠራዊት ይዞ የፋኑኤልን ጦር ተከተለ። "ዓቂም" (አማሬሳ) የሚል ስያሜ በተሰጠው ወንዝ ጋር ተገናኙ። በመካከላቸው ከፍተኛ ውጊያ ተደረገ። ኢማሙ መሀል ገብቶ ሠይፉን ከአፎቱ መዞ ከጠላት ጦር ጋር ገጠመ። ሌሎች በግራ አቅጣጫ የፋኑኤልን ጦር አጠቁ። ከራሱ ላይ የብረት መከላከያ ባጠለቀው ፋኑኤል የተመራው ጦር በቀኝ ክንፍ ባሉ ሙስሊሞች ላይ ጥቃት ከፈተ።
ኢማሙ አሕመድ የመጀመሪያው የሆነውን ጂሐድ በድል አድራጊነት ተወጣ። ከመስቀላዊያን የአፄዎች የጠላት ወገን 60 ፈረሰኞችና በርካታ እግረኞች ተማረኩ። በርካቶችም ተገደሉ። የጦር መሣሪያም ማረኩ። የተማረኩትን ሙስሊሞች አስለቅቀው በድል አድራጊነት ወደ ዚፋህ ከተማ ገቡ። የኢማሙ ገድልና ዝና ናኘ።
በአቅራቢያው የነበረው ሱልጣን አቡበክር ከአካባቢው ሸሸ። ኢማሙ አህመድ ባገኘው ድልና ምርኮ ተናደደ።
ሱልጣን አቡበከርና ኢማሙ አህመድ ጦርነት ገጠሙ። ሱልጣኑ ተሸንፎ ሸሸ። ኢማሙ ወደ ሐረር ከተማ ገባ። ሱልጣኑ በርካታ ሠራዊት መልምሎ ኢማሙ አህመድን ለማጥቃት ተመመ። ኢማሙ ደግሞ ሐረርን ለቅቆ ወደ ሁበት ሸሸ። የሱልጣኑ ጦር ተከተለው። ኢማሙ በሁበት ተራራ ላይ ወጣ። የሱልጣኑ ጦር ተራራውን ከበበ። ለሁለት ሳምንታት አላንቀሳቅስ አለ። በዚህ የተሰላቸው የኢማሙ ጦር በማታ ከተራራው ወረዶ ጦርነት ገጠሙ። ከኢማሙ አህመድ ጦር ውስጥ አሚር የነበረው ዑመረዲን ተገደለ። ኢማሙና ተከታዮቹም ወደየቀያቸው አቀኑ።
በኢማም አሕመድና በሱልጣን አቡበክር መካከል በዑለሞች አማካኝነት ስምምነት እንዲፈጠር ተደረገ። በስምምነቱ መሠረት ኢማሙና ሠራዊቱ የሱልጣኑን ጦር እንዲቀላቀሉ ተደረገ። ሱልጣኑም ሸሪዓን ሊጠብቅ ተስማሙ። ሆኖም ስምምነቱ ከጥቂት ቀናት በላይ አልዘለቀም። ሱልጣን አቡበክር ኢማም አሕመድን ለመግደል ማሤር ጀመረ። ስምምነቱ በሱልጣኑ ተጣሰ። ሱልጣኑ ኢማሙ አህመድን ሊገድል በመፈለግ ያለበትን ለማወቅ በየስፍራው ሰላዮችን ላከ። ዛዕካ መኖሩን ሰምቶ ጦር ላከበት። የኢማሙን ቤት አቃጠሉ። ንብረቱንም ዘረፉ። ሆኖም ኢማሙ አህመድን ሊያገኙት አልቻሉም።

ኢ ን ሻ አ ላ ህ ይ ቀ ጥ ላ ል

━━━━━━━━━━━━━━━ ኢማሙ አህመድ አልጋዚ         ክፍል :1━━━━━━━━━━━━━━━ሚናራው   ተነቅሎ  በመስጂድ   ሲቀደስኢስላም    ተጠልሽቶ   ኩፍርና   ሲወደስሙዕሚኑ    በ...
24/03/2022

━━━━━━━━━━━━━━━
ኢማሙ አህመድ አልጋዚ ክፍል :1
━━━━━━━━━━━━━━━

ሚናራው ተነቅሎ በመስጂድ ሲቀደስ
ኢስላም ተጠልሽቶ ኩፍርና ሲወደስ
ሙዕሚኑ በምነቱ ሲጎድፍ ሲራከስ
ሲጋልብ የመጣ በወርቃማው ፈረስ
አህመድ አልጋዚ ነው የሙስሊሞች ንጉስ
ህዝብ ታሪኩን ሲዘነጋ የጠላቱን ማንነትም እንደሚረሳ እናስታውስ ላመኑት ይጠቅማልና ማስታወስ፡፡
ድክም ባለ ጉልበታቸው ዳገቱን ወጥተው እንዳበቁ ዛፉን ደገፍ ብለው አረፍ አሉ። ሰውነቷን በምርኩዝ አሳርፋ ከኋላ የምትከተላቸው ባለቤታቸው ከጎናቸው ተቀመጠች። አብሯቸው ያለው ጎልማሳ ወዲያ ማዶ የሚታየውን ቤተክርስቲያን እየጠቆማቸው "ያ! የምታዩት ቤተክርስቲያን ሚኒሊክ ፈረስ መጋላ መስጂድን አፍርሶ የገነባው ነው" ብሎ በተሰበረ ልብ አንገቱን ወደመሬት አቀረቀረ። አዛውንቶቹ ባልና ሚስት ዓይናቸው እንባ እንዳቀረረ እርስ በርስ ተያዩ።
"...ሀረር ላይ የንጉሳቸውን አንገት ቆርጠን እንዳልሰቀልን ሚናራ ንደው መስቀል መትከል ቻሉ?!" አሉ አሮጊቷ በመገረም። "ባቲ" አሉ ሽማግሌው ድክም ባለ ድምጽ ፈረስ መጋላ መስጂድ ፈርሶ የተገነባውን መድሀኔአለም ቤተክርስቲያን በትካዜ እየተመለከተች "አቤት ኢማም" ብላ መለሰች። "ትዝ ይልሻል ያኔ ከቤተመንግስታችን ተቀምጠን ሙስሊሞች ከአንደሉስ ተባረው መስጂዶች ወደቤተክርስቲያን የመቀየራቸውን ታሪክ እየሰማን እንበሳጭ የነበረውን?" ብለው ኢማም አህመድ ወደሰማዩ አንጋጠጡ። ባቲ ድልወምበሯ በዓይን ተከትላ እንባ በደበዘዘው እይታ ሰማዩን እየቃኘች" እንደዛሬ ነው የማስታውሰው!" አለቻቸው። "በወጣትነቴ አባትሽ ኢማም ማህፉዝና የጦር መሪዬ ገራድ አቡን ሲጨዋወቱ እሰማው የነበረው እውነት አለ። ኡማው በዱንያ ፍቅር ልቡ ከተረታና ኢስላምን ችላ ካለ በበታቾቹ ይዋረዳል። የአንደሉስ እና የሐረር መስጂዶች ቤተክርስቲያን ቢሆኑ... ሀቅ የያዙት አንቀላፍተው ባጢል አይሎባቸው ነው። ጎልማሳው የሚሰማውን በወጉ እየተረዳ አልነበረም።
ኢማም አህመድ "እስቲ ጦልሀ ካቆምክበት ቀጥልልን" አሉት። ጦልሀ ጉሮሮውን በመጠራረግ ወጉን ቀጠለ "...እንዳልኳችሁ ሐረርን ለመውረር ምኒልክ በህዳር 12 ቀን 1886 ተነሳ። የጉዞውን ዓላማ ከሠራዊቱ በመደበቅ ከእንጦጦ ተንቀሳቀሰ። በሠራዊቱ መካከልም "አርሲ ያለው አጎቱ ራስ ዳርጌን ክረምት ከመግባቱ በፊት ለመገናኘት ነው" የሚል ወሬ ተናፈሰ። ታህሳስ 24 ቀን ገባያ ወንዝ ዳር ሠራዊቱን አሠፈረ። ይህን የሰሙት አሚር ዐብዱላሂ ሐረርን ለመከላከል ቆረጡ። ሐረር ማለት ማንነታቸው፣ ታሪካቸው፣ ህልውናቸው፣ እምነታቸው እና ክብራቸው ናት። ሙስሊሞችን ሁሉ ለጂሃድ ጠሩ። በሁለት ቀናት ውስጥ ሐረሪዎችን፣ ሱማሌዎችን እና ኦሮሞዎችን፣ ሁሉንም ሙስሊም ለጂሃድ አስነሱ። አብዛኛው ከኛ ከሙስሊሙ ሠራዊት ለእምነቱና ማንነቱ ሊሞት ቆርጦ የተነሳ ወዶ ገብ ሠራዊት ነበር። አዲስ ትዳር የያዙ ሙሽሮች ሁሉ "እምነቴ፣ ማንነቴ፣ ባህሌ፣ ታሪኬ፣ ሁሉም ነገሬ ኢስላም ነው። እኔ እያለሁ እንዴት እስልምናዬ ይደፈር?" በሚል ስሜት አዲሱን ጎጇቸውን ጥለው ለጂሃድ ተሰለፉ።
አሚር ዐብዱላሂ ሙስሊሙን በማስተባበር ለወረራ የመጣውን የምኒልክን ጦር ሊገጥሙ ባላቸው አቅም ተዘጋጅተው "ወራቢሌ" በሚሰኝ ስፍራ ጠበቁ። አፄ ምኒልክ ጥር 2 ቀን ለገና መዋያ ከአካባቢው ሕዝብ ሠራዊቱ እህል እንዲዘርፍ አዘዘ። የክርስቲያኑ የምኒልክ ጦር ለዘረፋ ወደ ኢቱ ኦሮሞዎች መሬት ተሰማራ። የምኒልክ ጦር ለወረራ ሲመጣ ከኛ ከሐረሪዎች ጋር ለትግል የተሠለፉት ኖሌ፣ ጃርሶ፣ ጊሪ፣ ሐበር አወል፣ ባቢሌ፣

23/03/2022

አንድ ታሪክ ለረመዳን ስንቅ 2

እግሩ ላይ የበቀለው እጢ ወደ ካንሰር በሽታ ተለውጦ አልጋ ላይ አውሎታል። ወደ ሌላ የሰውነት አካሉ እንዳይዛመት መቆረጥ እንዳለበት ሀኪሞች ወስነዋል። በወቅቱ ማደንዘዣ ስላልነበር ራሱን እስኪስት መጠጥ ጠጥቶ እንዲሰክርና ራሱን ሲስት ሊቆርጡት ፈልገው ሀሳቡን አቅርበውለታል። የእሱ መልስ ግን "በፍፁም ነበር" "ባይሆን ..." አለ "ባይሆን ለሰላት ቆሜ ሱጁድ ስወርድ ሀሳቤ ሁሉ በአኼራ ጉዳይ ስለሚወጠር የዚያኔ ቁረጡት" አላቸው።

ሀኪሙ ሱጁድ ሲወርድ ጠብቆ እግሩን በመጋዝ ይገዘግዘው ጀመር። ደም በብዛት ከሰውነቱ በመፍሰሱ ራሱን ስቶ ተዘረረ። ሲነቃ የተቆረጠውን እግር ይዞ እያለቀሰ ለእግሩ እንዲህ ይል ጀመር
"በአላህ እምላለሁ አንድም ቀን ወደ ሀራም ቦታ ሄጄብህ አላውቅም ለሊት ቆሜብህ ስሰግድ የማድረውን አላህ ፊት ምስክር ትመሰክራለህ" አለ ዑርዋ ኢብኑ ዙበይር።
ከጎኑ የነበረ አንድ ሰሀባ "አብሽር ይህ ቁራጭ አካልህ ጀነት ቀድሞህ ገብቷል ኢንሻ አላህ" በማለት አፅናናው።

ለተከበረው ረመዳን አላህ በሰላም ያድርሰን

23/03/2022

╔══════════════════╗
አንድ ታሪክ ለረመዳን ስንቅ 1
╚══════════════════╝

ጌታዬ ሆይ!
ብዕሬን እንደ ኻሊድ ኢብኑል ወሊድ ሠይፍ የሰላ አድርግልኝ
Hamzi hamza

ያኔ በደጋጎቹ ጊዜ በምርጥ የአላህ ባሮች ዘመን ቤት ውስጥ የምታገለግል አንዲት ሴት ባርያ ነበረች፡፡ አሳዳሪዋ በገንዘብ እጦት ሽጣትና ወደ ገዟት ቤተሰብ አቀናች። እኩለ ለሊት ላይ ተነሳች
"እናንተ ቤተሰቦች ሆይ!… ሰላት! … ሰላት!.." ስትል ተጣራች፡፡ ከእንቅልፋቸው እየባነኑ "ፈጅር ደረሰ?" ሲሉ ጠየቋት፡፡ "እናንተ ከግዴታ ሰላት ውጭ አትሰግዱም እንዴ?" አለቻቸው። አዎ ሱብሂ ሲደርስ ቀስቅሽን ብለዋት ተኙ። በጣም አዘነች። ምን አይነት ቤት ነው የገባሁት አለች።

ወቅቱ የረመዳን ወር የተቃረበበት ነበርና ጠዋት እንደነጋ አሳዳሪዎቿ ጣፋጭ ምግቦችንና ለስላሣ መጠጦችን ሲያዘጋጁ ተመለከተች፡፡ ድግስ አለባችሁን በማለት ጠየቀች
"በፍፁም ለረመዳን ፆም እየተዘጋጀን ነው" ሲሉ መለሱላት፡፡ እጅግ በጣም ተገርማ አይኗን አቁለጨለጨች "ረመዳንን ብቻ ነው እንዴ የምትፆሙት" ንግግሯን ቀጠለች "ዓመቱ ሙሉ ረመዳን የሆነበትን ቤት ትቼ እናንተ ዘንድ መጣሁ እባካችሁ ወደ እነኛ ደጋግ ሠዎች መልሱኝ" ስትልም ተማፀነቻቸው፡፡
መለሷት። ወደ ቀድሞ አሳዳሪዋ ቤት ሄደች፡፡
"ለክፉ ሰዎች ሸጥከኝ ከግዴታ ሶላት ውጭ አይሰግዱም። ሆዳቸውን እንጂ ለኢማናቸው አይሰንቁም እባክህን መልሰኝ" በማለት እያለቀሰች ትማፀን ያዘች።

ሙሉ የሕይወት ዘመናቸው ረመዳን የሆነላቸው የአላህ ምርጥ ባሮች በየዘመኑ አሉ፡፡ ሁሉንም የዱንያ ቀናት ረመዳንን የሚወዱትን ያህል የሚወዱ፡፡ አላህ በሰላም ያድርሰን

╔═══════════════╗
ኢኽላስ - ታማኝነት - ትጋት - ስኬት
╚═══════════════╝
ጌታዬ ሆይ! ባልሰራበት እንኳ ወደ መልካም ነገር ያመላከተ ሰው የሚያገኘውን አጅር አታሳጣኝ

Address

Bahir Dar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ታሪካችንን እንወቅ islamic channel posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share