23/12/2020
"ጃቢር (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት፡- እሳቸው (ጃቢር)ከአሏህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) ጋር ወደ "ነጅድ" አቅጣጫዘመቱ፡፡ መልዕክተኛው (ሶ.ዐ.ወ) ከዘመቻ ሲመለሱእሾሃማ ከሆነ ሸለቆ አካባቢ ሲደርሱ የእኩለ ቀን የእረፍትሰዓት (ቀይሉላ) ደረሰባቸው፡፡ እዚሁ ስፍራ ላይ ሰፈሩ፡፡ሰዎች በየዛፎቹ ጥላ ስር ተጠለሉ፡፡ የአሏህ መልዕክተኛ(ሶ.ዐ.ወ) ከአንድ እሾሃማ ዛፍ ጥላ ስር አረፉ፥ ጦራቸውንከዛፉ ላይ አንጠልጥለው፡፡ እንቅልፍ አሸለበን፡፡ ብዙምሳይቆይ የአሏህ መልዕክተኛ ጠሩን፡፡ አንድ"አዕራቢይ" (ገጠሬ) ከጎናቸው አለ፡፡ "ይህ ሰው ተኝቼእያለሁ በኔ ላይ ጎራዴ መዘዘ፡፡ ሾተን ከአፎቱ መዞ አየሁት፡፡"ከእኔ ማን ያድንሃል?" አለኝ፡፡ "አሏህ" አልኩት ሶስትጊዜ፡፡" ካሉ በኋላ ተቀመጡ፡፡ አልተቆጡትም፡፡ (ቡኻሪናሙስሊም ዘግበውታል)በሌላ ዘገባ ደግሞ ጃቢር እንዲህ ሲሉ ማስተላለፋቸውተወስቷል፡-• "ዛተ አር-ሪቃዕ" በተባለ ዘመቻ ወቅት ከአሏህመልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) ጋር ነበርን፡፡ ጥላማ ከሆነ ዛፍደረስን፡፡ ለአሏህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) ተውንላቸው።አንድ አጋሪ ሰውዬ መጣ፡፡ የአሏህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ)ጎራዴ ከዛፉ ላይ ተንጠልጥሏል፡፡ ጎራዴውንበመልዕክተኛው ላይ አነጣጠረና፡- "ትፈራኛለህ?"አላቸው፡፡ "አልፈራህም" ሲሉ መለሱለት፡፡ "ከኔ ማንያድንሃል?" አላቸው። "አሏህ" አሉ፡፡አቡበክር ኢስማዒል ባስተላለፉት ሶሒሕ ዘገባ ደግሞ፡-"ከኔ ማን ያድንሃል?" አላቸው፡፡ "አሏህ" አሏት፡፡ ጎራዴውከእጁ ወደቀ። የአሏህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) ጎራዴውንያዙና፡- "ከኔ ማን ያድንሃል?" አሉት፡፡ "ክፉን በክፉየማይመልስ ደግ ወዳጅ ሁን" አላቸው፡፡ "ከአሏህ ሌላአምላክ አለመኖሩንና እኔ የአሏህ መልዕክተኛ መሆኔን ትመሰክራለህን?" አሉት፡፡ "ይህንን አልፈፅምም፡፡ ግናካንተ ጋር ላልዋጋና አንተን ከሚወጉህ ሰዎች ጋር ላላብርቃል እገባለሁ" አላቸው፡፡ ከባልደረቦቹ ዘንድ ሄደና፡-"ከሰው ሁሉ ይበልጥ ደግ ከሆነ ሰው ዘንድ ነበርኩ"አላቸው፡፡ - ቡኸሪ ዘግቦታ"
==========================================
ሼር ሼር ሼር ሼር ሼር ሼር ሼር ሼር
Like like like like like like like