23/03/2021
የፕሮቻዝካዊያን ሚኒሊካዊ ፎቢያ
--------------------
ዝነኛው የአማራ ልዩ ሀይል ባይኖር፦
በእርግጥም ተወርዋሪው ኮከብ የአማራ ልዩ ሀይል ባይኖር ኑሮ ዛሬ አብይ አህመድ በስሟ የስልጣን ወንበሯ ላይ ቁጭ ያለባት ኢትዮጵያ አትኖርም ነበር። ዘንጦ ለብሶ የፓርላማ(የሕዝብ እንደራሴ) ወንበር ላይ መቀመጥም አይገኝም ነበር። በፅኑ የሀገር ፍቅር ታንፆና ተክትኩቶ የተሰራው የአማራ ልዩ ሀይል በብርሃን ፍጥነት ተምዘግዝጎ ከበባ ውስጥ የነበረውን የሀገር መከላከያ የሰሜን ዕዝ 5ኛ ሜካናይዝ ክፍለ ጦር መታደግ ባይችል ኖሮ ዛሬ አብይና ባልደረቦቹ በስልጣን ላይ ስለመገኘታቸው አጠራጣሪ ነበር።
~
በእርግጥ የአማራ ልዩ ሀይል አገርን ከብተና ለመታደግ ያደረገው ተጋድሎና የዋለው ውለታ ከጭንቅ ባስመለጣቸው የመከላከያ አባላት ምስክርነት የተቸረው ነው። ያ ድንቅ ውለታ መንፈቅ ሳይሞላው በፕሮቻስካ የመንፈስ ልጆች በክህደት ተደምድሟል። ሀገርን የታደገበት ፍጥነቱ ጥበቡና ጀግንነቱ ግን በዕንቁ የታሪክ መዝገብ ተመዝግቦ ሲታወስ የሚኖር እንጅ የሚደበዝዝ አይደለም። ባለድሉ የአማራ ልዩ ሀይልጨየተፃፈው ደማቁ ታሪክ ሲያበራ ይኖራል።
የዘመኑ ፕሮቻዝካዊያን፦
ከአድዋ ድል ማግስት በድል አድራጊው ንጉስ ሚኒልክና በኢትዮጵያዊው የምኒልክ ሰራዊት አሸናፊነት የተቃጠለው ፕሮቻዝካ አማራ የጠላበትና ጭራቅ አድርጎ ለመሳል በአውሮፓ ልሳነ ምድር የተንከራተተው ነጭ ተሸንፎ እምዬ ምኒልክና ሰራዊቱ አገርን ከቅኝ ግዛት በመታደረጉና አፈር አስግጦ ድል በማድረጉ ነበር። ነጭ ተሸናፊነቱ ምኒሊክና ሰራዊቱ ድል አድራጊነቱ የአለም መነጋገሪያ ሲሆን አይኑ የቀለው አውስትሪያዊ ፀረ አማራ ትርክቱን በነጭ ሰማይ ስር ዘራ። አገር የታደገውን ንጉስና የንጉስ ሰራዊት አብጠለጠለው። አገርን ትናንትናና ነበር እንዳይኖራት የመጣው ወራሪ ተሸነፈ፤ ምኒልክና ሰራዊቱ አሸነፈ፤ ያን ነጭ ፕሮቻስካም የበታችነት ስሜት ውስጡን አነደደው። የጥላቻውን ዘርም ዘራ።
~
ዛሬም ሀገርን የታደገው በአማራ ሀይል የሚነዛው ጥላቻ አስገራሚ ነው። ሀገርን በጀግንነት በመታደጉ ዝናው ናኝቷል። ይሔን መልካም ዝና መጎናፀፉ ያበሳጫቸው እኩዮች ራሳቸው በከፈቱት ጦርነት ላይ አማራንና ሰራዊቱን እንደ ጭራቅ ለመሳል እየቧጠጡ ነው። ዛሬ በኢትዮጵያ ሰማይ ስር በይስሙላው የሕዝብ እንደራሴ ስብስብ በአሸናፊውና ድል አድራጊው የአማራ ልዩ ሀይል ላይ ሲፈፀምበት የነበረው ውንጀላና ክስ በሚዛን ሲመዘን ከፕርቻስካው ውንጀላ በእጅጉ የባሰ ነው። የሚያመሳስለው ድል አድርጎ ሀገር የታደገን ሀይል በበታችነት ስሜት በመናወዝ ከድል ማግስት ውንጀላ ውስጥ መገባቱ ነው።
~
በአማራ ላይ ጦርነት ከፍቶ ያሻውን የፈፀመ ሀይል ምንም ሳይባል ክሱ ወደ አማራ መዞሩ ተገድለነም ሞታችን የማይነገርን ገደሉ የምንባል ስመ መራር ሕዝብ ሁነናል። የአማራ ልዩ ሀይል ንፁሃን ኦሮሞችን ገደለ የሚለው ክስ የመጣው ከአማራ ጠልነት ባሻገርም የአማራን ሀይል ለሀገረ መንግስቱ ያለውን ታማኒነት ጥርጣሬ ውስጥ ለማስገባት መሆኑ ግን ይገባናል። በኢትዮጵ ስም በተሰዬመው በይስሙላ እንደራሴ ውስጥ ከ78%እስከ 80% የሚሆነው ሕዝብ አማራ በሆነበት ልዩ ዞን የአማራ ልዩ ሀይል ከአማራ ክልል ይውጣ የሚሉ ድምፆችን ስትሰማ ደግሞ ነገሩ የበለጠ ፈገግ ያደርግሃል። ዛሬ የአማራ ልዩ ሀይል ላይ የጥላቻ ዶፍ ያዘነቡት በችሮታ በልዩ ዞንነት የተበረከተውን ዞን በሕዝብ ዕንደራሴነት የወከሉ እንደ ሰው ማሰብ የማይችሉ በምኒልክ ፎቢያ የነደዱ ሰው መሰል ዝንጀሮዎች ናቸው።
~
መሰሪያ፦
ለኔ ግን ትልቁ ቁምነገር ሰዎቹ እንዲህ መናገራቸው አይደለም። የማንም ቅርሻታም እየተነሳ በዚያ ድል አድራጊና ደማቅ ታሪክ በፃፈው ልዩ ሀይል ላይ የሚተፋውን ቅርሻት መስማት የሚያም ቢሆንም ተግባሩ ግን ከፕሮቻዝካውያን የሚጠበቅ ነውና ይሔ ድርጊት ብዙ አይገርመኝም። መሰረታዊው ጥያቄው ግን የአማራ ብልፅግና ቀጣይ ዕርምጃዎች ምን ይሆናሉ ምንስ መሆን አለባቸው፤ ከእያንዳንዳችንስ ምን ይጠበቃል የሚለው ነው። ይታሰብበት!!!
© Sisay Altaseb
more info cotact ustelegram :_https://t.me/joinchat/UOuKOg5cbcyIZKHFfascebook :-https://www.facebook.com/amarewfCopyright Disclai...