14/11/2022
መጽሐፍ ቅዱስ በዳንሳዊ እና ጩፋዊ አንድምታ ሲተረጎም ብልጽግና ወንጌል የወረሰው የMirackle money ምርኮኛ ትፈጥራለህ...
ይህ ህዝብ ኢየሱስ በሚለው ስም ላይ ረፍት ሊያደርግ፣ሰላሙን ሊያጭድ ሳይሆን ካዝናውን ሊሞላ የተጣደፈ ምስኪን ነጋዴ ህዝብ ሆኗል።
ክርስቶስን ከATM card ፍቅር በላይ ከፍ አድርጎ መመልከት ስለሚያቅተው በባዶ ቡክ ውስጥ ነዋይ ይሞላለት ዘንድ እንዲህ ተሰልፎ ይዳክራል።
ኢዩ ጩፋ የሰበከው ወንጌል እስራኤል ዳንሳ ያመሳጠረው ስብከት፣ዳዊት ሞላልኝ የተቀኘው ቅኔ ዳሩ ከእዚህ ውጪ ጣዕም እንደሌለው ሃቅ ቢሆንም .....ነገር ግን በጣም ፈጠነ።
ወደ ሰማይ አንጋጠህ ትቸነከራለህ እንጅ ያልሰራህበትን ድንቡሎ ሳንቲም ኢየሱስ አይሰጥህም ።
ይልቁንስ በክርስቶስ መከተል ውስጥ ፍጹምነትን ማግኘት ከወደድ“ ሂድና ያለህን ሸጠህ ለድሆች ስጥ፥ መዝገብም በሰማያት ታገኛለህ፥ ማቴ 19፥21" ብሎ ያለህን በቸርነት እንድትበትን ያደርግልሃል እንጅ ሚራክል መኒ ብሎ አኩኩሉ እሱ ጋ አይሰራም።
ከእዚህ ውጪ ያሉትን በፍቅረ ነዋይ የወደቁትን መጸሐፍ ቅዱስ በተክሳጽ ቃን "ገንዘብን መውደድ የክፋት ሁሉ ሥር ነው...ሲል ለክፋት የሚጣደፉትን ትውልድ መሆናቸውን ይገልጻል።— 1ኛ ጢሞ 6፥10"
ያ የቀራንዮ መከራ፣የጎልጎታ ስቃይ፣የሮም ወታደሮች አጥንት ድረስ ዘልቆ የሚሰማን ግፍ የተቀበለት የግርፋቱ ንቅሳት አንተን ኢንቬስተር ሊያደርግህ አይደለም።
ያ መመሪያ የሆነው የህይወት መጽሐፍ የክርስትናችን አካሄድ " ገንዘብን ያለ መውደድ ይሁን፥ ዕብ13፥5" ሲል አንቀጽ ሰራ እንጅ የብልጽግና ወንጌል የሚል የዳቦ ጥያቄ መመለሻ ተረት አልፈጠረም።
ይህን ትውልድ ግን የሚያነቃ ይጥፋ ?
Kune Demelash kassaye -Arba Minch