24/04/2026
እየየ ብቻ
በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ዞን ላይ ጋይንት ወረዳ ባለፈው አርብ ሚያዚያ 9/2018 ዓ.ም. ሳሊ በተባለች አነስተኛ ከተማ የመንግሥት ወታደሮች በፈፀሙት ጥቃት ሰባት ሠዎች መገደላቸውን እና ቤተ ክርስቲያን ላይ ጉዳት መድረሱን ቢቢሲ ያነጋገራቸው ምንጮች ገለፁ። ሟቾቹ ሁለት የቤተ ክርስቲያን ዲያቆናት፣ አንድ መርጌታ (የድጓ መምህር)፣ የእንስሳት ሐኪም እና ሦስት አርሶ አደሮች መሆናቸውን ተናግረዋል። አገልጋዮቹ ቀድሰው ሲወጡ ቤተ ክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ ሲገደሉ፤ ሦስቱ ሰዎች በቤታቸው እና አንድ ሰው ደግሞ መንገድ ላይ መገደሉን ቢቢሲ ያሰባሰባቸው መረጃዎች ይጠቁማሉ።https://bbc.in/4cprScn