22/07/2026
የአማራ ክልል ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ያዘጋጀውን በወንጀል መከላከል የመጀመሪያ ደግሪ እና የድህረ ምረቃ ዲፕሎማ ስርዓተ-ትምህርቶች ወርክሾፕ አካሄደ፡፡
ሀምሌ 14 2018 ዓ ም ደብረ ማርቆስ
የአማራ ክልል ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ለመጀመሪያ ጊዜ ያዘጋጀዉን በወንጀል መከላከል የመጀመሪያ ዲግሪና የድህረ ምረቃ ዲፕሎማ ስርዓተ-ትምህርቶች ላይ ከዩኒቨርስቲ ኮሌጁ አመራርና መምህራን ጋር ቫሊዴሽን ወርክሾፕ አካሂዷል።
በውይይቱ ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ፕሬዘዳንት ም/ ኮሚሽነር አበበ ደለለ እንዳሉት ተቋማችን ከኮሌጅነት ወደ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ማደጉን ተከትሎ አዳዲስና ያደጉ የስልጠና ፕሮግራሞችን መጀመር ይጠበቅብናል ብለዋል። በ2019 በጀት ዓመት ስልጠና ለመስጠት በዕቅድ ከተያዙት ውስጥ በወንጀል መከላከል የመጀመሪያ ዲግሪ እና የድህረ ምረቃ ድፕሎማ ስልጠና ፕሮግራሞች ዋነኞቹ በመሆናቸው በነዚህ የስልጠና ፕሮግራሞች ላይ የተዘጋጀ ስርዓተ-ትምህርቶች ላይ ከመምህራን ጋር መወያየትና አዳዲስ ሀሳቦችን በማመንጨት የክልላችንን ፖሊስ የመፈፀም አቅም የሚያሳድግ ስልጠና መስጠት አስፈላጊ በመሆኑ ነው ብለዋል ።
በመሆኑም የዩኒቨርስቲ ኮሌጁ መምህራን አዳዲስና ገንቢ ሀሳቦችን በማፍለቅ ስርዓተ-ትምህርቱን ማዳበር ይጠበቅባቸዋል ብለዋል። የዩኒቨርስቲ ኮሌጅ የጥናትና ምርምር ዋና መምሪያ ሀላፊና የአካዳሚክስ ጉዳዬች ምክትል ዋና ዳይሬክተር ተወካይ ምክትል ኮሚሽነር መላኩ ሲሳይ እደገለፁት በአዲሱ በጀት ዓመት በርካታ ስልጠናዎችን መስጠት የሚጠበቅብን ስለሆነ መምህራን ራሳቸዉን ከወዲሁ መዘጋጀት ያለባቸው መሆኑን ገልፀዋል።
የዛሬዉ የስርዓተ-ትምህርት ቫሊዴሽን ወርክሾፕ የ2019 በጀት ዓመት ዋና ተግባሮች ውስጥ በመሆናቸው የተዘጋጀውን ስርዓተ-ትምህርት ማዳበር የሚጠበቅብን ስለሆነ መምህራን ከፍተኛ ተሳትፎ እዲያደርጉ አሳስበዋል።
በመጨረሻም የተዘጋጁትን ረቂቅ ስርዓተ- ትምህርቶችን ዋና ኢንስፔክተር (እጬ ዶክተር ) ከፍያለው የኔየት አቅርበው በዩኒቨርስቲ ኮሌጁ አመራሮችና መምህራን ሰፊ ውይይት ተደርጎበት ወርክሾፑ ተጠናቋል።
በጀግንነት መጠበቅ በሰባዊነት ማገልገል።