20/06/2026
የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንት የምስጋና መልዕክት
********************************************
ቢሾፍቱ ፣ ሰኔ 13 ፣ 2018(ኢመዩ)በኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ከሰኔ 4 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ ለቅድመ ምረቃ ተማሪዎች የተሰጠው የመውጫ ፈተና በከፍተኛ ቅንጅት፣ በጠንካራ ዝግጅትና በሙሉ ኃላፊነት መጠናቀቁን በማስመልከት የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ምክትል ኘሬዝዳንት ተስፋዬ ቶሉ(ዶ/ር) የምስጋና መልዕክት አስተላልፈዋል።
ዩኒቨርሲቲው ከመውጫ ፈተና ጋር በተያያዘ በርካታ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ሲያከናውን መቆዩቱን ያስታወሱት ዶ/ር ተስፋዬ ፣ በፈተናው ወቅትም አስፈላጊው ሁሉ ድጋፍና ክትትል መደረጉን ገልፀዋል።
ለዚህ ሀገራዊ ኃላፊነት ስኬት የጎላ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የዩኒቨርሲቲው የመውጫ ፈተና ግብረ ኃይል፣ አካዳሚክና አስተዳደራዊ አመራሮች፣ መምህራን፣ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት እና የትምህርት ሚኒስቴር የፈተና ማዕከል አስተባባሪዎች፣ የአይሲቲ ባለሙያዎች፣ የፌዴራል ፓሊስ ና የዩኒቨርሲቲው የፀጥታ አባላት፣ የጤና፣ ሎጂስቲክስና ድጋፍ ሰጪ ክፍሎች እንዲሁም በሂደቱ የተሳተፉ ሁሉንም ባለድርሻ አካላት በዩኒቨርሲቲው ስም አመስግነዋል።
የዘንድሮው የመውጫ ፈተና በሥነ-ሥርዓት፣ ግልፅ በሆነ መንገድ መከናወኑ፣ ዩኒቨርሲቲያችን የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥና ብቁ ወታደር ሙያተኞችን ለማፍራት ያለውን ጽኑ ቁርጠኝነት በተግባር ያረጋገጠ እንደሆነ ምክትል ኘሬዝዳንቱ በመልዕክታቸው አስረድተዋል።
ወደፊትም ዩኒቨርሲቲያችን ከትምህርት ሚኒስቴር ፣ ከትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት እና ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር በተጠናከረ ትብብር በመስራት የትምህርት ጥራትን፣ የፈተና ታማኝነትንና የተቋሙን አካዳሚክ ልቀት ለማጠናከር ያለውን ጥረት በተከታታይ ያጠናክራል ።
በመጨረሻም ፈተናውን ለወሰዳችሁ ተማሪዎች ሁሉ ከልብ እንኳን ደስ አላችሁ፤ የለፋችሁበት ጥረት በተገቢው ውጤት እንዲከበር እመኛለሁ። በሙያችሁ የሀገራችንን ልማትና የመከላከያ ተቋማትን በብቃትና በታማኝነት እንደምታገለግሉ ሙሉ እምነት አለኝ።
ዶ/ር ተስፋዬ ቶሉ
የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ
አካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንት
ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን!
የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ
telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenceUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni
📌tiktok
👇👇👇👇
https://www.tiktok.com/