12/08/2026
የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ
ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ የብቃት ምዘና ፈተናውን ለመውሰድ ምዝገባ ያጠናቀቃችሁ የጤና ባለሙያዎች በሙሉ፤ ፈተናው ከነሀሴ 13 እስከ 15/2018 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑን እየገለፅን፦
1.የፈተናው መርሃ-ግብርም፦
-በ13/12/2018 ዓ.ም…… Medicine, Pharmacy, Anesthesia, Environmental Health, Human Nutrition, Emergency and Critical Care Nursing, Dental Medicine እና Optometry
-በ14/12/2018 ዓ.ም…………, Medical Laboratory Science, Public Health, Midwifery, Medical Radiology Technology, Pediatric and Child Health Nursing, Psychiatric Nursing, Physiotherapy እና Surgical Nursing
-በ15/12/2018 ዓ.ም…… Nursing
ሁሉም ተፈታኝ ነሀሴ 12/2018 ዓ.ም ከሰዓት 8፡00 ሰዓት በመፈተኛ ጣቢያ በመገኘት ስለፈተናው አሰጣጥ ቅድመ ገለጻ (orientation) መከታተል፤ የቅድመ ፈተና መለማመጃ ጥያቄዎችን መስራትና፤ የመፈተኛ ክፍሉን መለየት ይኖርበታል::
2.በፈተናው ወቅት የብሄራዊ መታወቂያ (National ID) እንዲሁም ሲስተሙ የሚሰጠውን QR code ያለው የፈተና መግቢያ /ስሊፕ/ print out ይዛችሁ መገኘት ይኖርባችኋል፡፡
3.ከላይ ከተጠቀሱት ነገሮች ውጪ ምንም አይነት የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ (ስልክ፣ የእጅ ሰዓት፣ መነጽር (የተረጋገጠ የዕይታ ችግር ከሌለ በስተቀር)፣ ቦርሳ እና ሌሎች እቃዎች፣ ምንም አይነት ማጣቀሻዎችን፣ እንዲሁም ባዶ ወረቀቶች፣ ምግብ ወይም መጠጥ (የተረጋገጠ የጤና ችግር ከሌለ በስተቀር) ይዞ መግባት አይፈቀድም፡፡
4.በፈተናው ወቅት ተመዛኞች በሁለቱም ክፍለ ጊዜ (ጠዋት እና ከሰዓት በኋላ) የፈተና ክፍሉን ለቀው ከመውጣታቸው በፊት አቴንዳንስ ላይ በአግባቡ መፈረም ይጠበቅባቸዋል፡፡
5.በተጨማሪም ከስር የተያያዘውን የፈተና ሂደቱን የሚያሳይ ቪዲዎ መመልከት የምትችሉ መሆኑን እናሳስባለን፡፡
6.ተመዛኞች ወደ ጣቢያ ከመምጣታችሁ በፊት ከዚህ ማስታወቂያ በታች የተያያዘውን ዚፕፋይል በመክፈት የመረጣችሁትን የፈተና ጣቢያ መመልከት ይኖርባችኋል።
ማሳሰቢያ፦
ተመዛኞች ስማቸው ከተጠቀሰበት የመፈተኛ ጣቢያ (ተቋም) ውጪ በፍጹም ፈተናውን መውሰድ አይፈቀድም፡፡
ዳንዲቦሩ ኮሌጅ ደሴ ካምፓስ
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
በቴሌግራም_አድራሻችን👇'
=> https://t.me/dandiiborudc
በfacebook_አድራሻችን👇
=> https://fb.me/DBCDC
በዩቲዩብ_አድራሻችን👇
=>https://www.youtube.com/
በኢንስታግራም አድራሻችን፡👇
=>https://www.instagram.com/dandiiborudc/ #
በኤክስ አድራሻችን፡ 👇
=>https://x.com/dandiiborudc
በቲክቶክ አድራሻችን፡ 👇
=>https://www.tiktok.com/