Dilla University

Dilla University It is an academic institution in Ethiopia.

በዩኒቨርሲቲው የሰለጠኑ ከ300 በላይ የስቴም ማዕከል ሰልጣኞች ተመረቁ===========***********===========ዲ.ዩ: ነሐሴ 30/2018ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)በዲላ ዩኒቨርሲቲ በ2018...
05/09/2026

በዩኒቨርሲቲው የሰለጠኑ ከ300 በላይ የስቴም ማዕከል ሰልጣኞች ተመረቁ
===========***********===========

ዲ.ዩ: ነሐሴ 30/2018ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)

በዲላ ዩኒቨርሲቲ በ2018ዓ.ም በተለያዩ የሳይንስ ዘርፎች በስቴም ማዕከል የሰለጠኑ ከ300 በላይ ሰልጣኞች ተመርቀዋል።

የዲላ ዩኒቨርሲቲ የኢንዱስትሪ ግንኙነት እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ዳይረክተር አዲሱ ፍርንጆ (ዶ/ር) ባደረጉት ንግግር፣ ማዕከሉ ባጠቃላይ ከ3500 በላይ ተማሪዎችን አሰልጥኖ ማስመረቁን እና የማዕከሉ ምሩቃንም ባሁኑ ጊዜ ጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኙ ገልፀዋል።

አክለውም በዛሬው ዕለት የተመረቁ ከ300 በላይ ተማሪዎች በክረምት፣ በሳምንቱ መጨረሻ እንዲሁም በጂኦስፖሻል ስልጠናና በተለያዩ ዘርፎች ስልጠናውን ተከታትለው ለምረቃ መብቃታቸውን ጠቁመዋል።

ማዕከሉ ጥራት ያለው ስልጠናዎችን ስለሚሰጥ፣ ባሳለፍነው ዓመት በEmerging technology በሀገር አቀፍ ደረጃ ሁለተኛ ደረጃ ይዞ ማጠናቀቁን ጠቁመው፣ ተማሪዎች የሳይንስ ፈጠራ እውቀታቸው እንዲጎለብት ዩኒቨርሲቲው የተለያዩ ድጋፎችን እያደረገ እንደሚገኝ አውስተዋል።

ሰልጣኞች እዚህ ያገኙትን እውቀት ወደየ ትምህርት ቤቶቻቸው ሲመለሱ ለሌሎችም እንዲያካፍሉ እና የሳይንስ ፈጣሪ ዜጎችን እንዲፈጥሩም አደራ ብለዋል። በቀጣይ ዓመት ወደ ማዕከሉ ሲመጡም አዳዲስ ፕሮጀክቶችን ይዘው እንዲመጡ ዳይሬክተሩ አሳስበዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘላለም ጳውሎስ በበኩላቸው፣ የጅኦስፓሻል ስልጠና በሀገር እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ዜጎችን ለመፍጠር ባለድርሻ አካላት ተባብረው ያዘጋጁት እንዲሁም የሚደግፉት ስልጠና መሆኑን አውስተዋል። ዲላ ዩኒቨርሲቲ በዚህ ረገድ ተጽህኖ ፈጣሪ ዜጎችን እየፈጠረ እንደሚገኝ ገልፀው፣ ዩኒቨርሲቲው በትውልድ ላይ እየሰራ ላለውና እየተመዘገበ ላለው የሚጨበጥ ለውጥ በክልሉ ስም አመስግነዋል።

በተለይ በክረምቱ የተሰጠው የጂኦስፓሻል ስልጠናን በየዓመቱ ለመስጠት እቅድ ስለመኖሩ የገለፁት ኃላፊው፣ የሰለጠኑ ተማሪዎች እድሉን ላላገኙ ወንድሞቻቸው ያገኙትን እውቀት እንዲያገሩ አደራ ብለዋል።

የጌዴኦ ዞን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ መምሪያ ኃላፊ አቶ ደረጄ ሾንጣ ተመራቂ ተማሪዎችን እንኳን ለምረቃ ቀናችሁ አደረሳችሁ ብለዋቸዋል። ኃላፊው አክለውም በዚህ ጊዜ ላይ ዓለም በቴክኖሎጂ ዘርፍ ውድድር ላይ እንደምትገኝ ጠቁመው፣ ኢትዮጵያ በዚህ ዘርፍ ላይ በዓለም ደረጃ ተወዳዳሪ ለመሆን በልዩ ትኩረት እየሰራች ትገኛለች ብለዋል።

ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ ጊዜያት ላይ እንደ ሀገር የተያዘው እቅድ ከግብ እንዲደርስ የበኩሉን ሚና እየተወጣ እንደሚገኝ አውስተዋል።

ወቅቱ ቴክኖሎጂ የየለት ስራዎቻችን ጋር የበለጠ የተቆራኘበት በመሆኑ፣ ተማሪዎች ከዚህ ሲመለሱ ማህበረሰቡ ጋር ያሉ ችግሮችን በቅርበት በመከታተል ንድፈ ሀሳብ በማዘጋጀት ችግር ፈቺ ፕሮጀክቶችን እንዲያስቡ ጥሪ ያቀረቡት ኃላፊው ዞኑ እንዲሁም በየደረጃው የሚገኙ አካላት ድጋፍ እንደሚያደርጉ አውስተዋል።

በመድረኩ ለ45 ቀናት በስፔስ እና ጂኦስፓሽያል ዘርፍ ላይ ስልጠና ሲወስዱ የነበሩ ተማሪዎችም ተመርቀዋል። በስልጠናው ወቅት ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች የእውቅና የምስክር ወረቀት እና የማበረታቻ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

=== # # #===



05/09/2026

Dilla
04/09/2026

Dilla

መላው የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች እንኳን ለ2019ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሰላም አደረሳችሁ!የወደፊት ህልምዎን እውን ለማድረግ ዲላ ዩኒቨርሲቲን መርጠው እንዲማሩ የከበረ ጥሪያችንን እናቀርባለን!...
04/09/2026

መላው የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች እንኳን ለ2019ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሰላም አደረሳችሁ!

የወደፊት ህልምዎን እውን ለማድረግ ዲላ ዩኒቨርሲቲን መርጠው እንዲማሩ የከበረ ጥሪያችንን እናቀርባለን!

ዲላ ዩኒቨርሲቲን ተመራጭ የሚያደርጉ አንኳር ምክንያቶች

📍ሰላማዊ እና ምቹ አከባቢ ላይ መገኘቱ
📍በመማር ማስተማር ስነ ዘዴው በብዙዎች የተመሰከረለት የትምህርት ጥራት አምባሳደር መሆኑ
📍 በቂ እና ዘመኑን የዋጀ የICT መሠረተ ልማት የተሟሉለት መሆኑ
📍ጥራት ባላቸው እና በዘመናዊ የቴክኖሎጂ ግብዓቶች የተደራጁ የስማርት መማሪያ ክፍሎች ባለቤት መሆኑ
📍በቂ እና ልምድ ባላቸው ምሁራን ትምህርት እየሰጠ መሆኑ
📍ዘመናዊ የመማሪያ ቤተሙከራዎች የተደራጁለት መሆኑ
📍በገበያው ላይ ተፈላጊ የሆኑ በርካታ የትምህርት ዓይነቶችን የሚያስተምር መሆኑ እውነትም ተመራጭ ያደርገዋል።

ዲላ ዩኒቨርሲቲ የሚገኝበት ዲላ ከተማም ለኑሮ ተስማሚ፣ እጅግ ተመራጭ እና ተወዳጅ መሆኗ፣ ተቋማችንን መርጠው የሚመጡ ተማሪዎችን እውነትም እድለኛ ያደርጋቸዋል።

የዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት እና የአከባቢው ማህበረሰብም 'ትንሿ ኢትዮጵያ' ወደሆነው አንጋፋው ተቋማችን ስትመጡ፣ ሁሉን አቀፍ ድጋፍና ትብብር ለማድረግ ዝግጁ ናቸው።

🎯 ኑ ህልምዎን እውን ያድርጉ፣ ያተርፉበታል።
🎯 መረጃውን ለጓደኞችዎ ያጋሩ!

ዲላ ዩኒቨርሲቲን ይምረጡ!

=== # # #===


!


 #የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ  #ከነሐሴ 28/2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜን 05/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ መሆኑ ተጠቆመ! በ2018 ዓ.ም የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሀገር ...
04/09/2026

#የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ #ከነሐሴ 28/2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜን 05/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ መሆኑ ተጠቆመ!

በ2018 ዓ.ም የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ በመደበኛው የትምህርት መርሐግብር የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ እንድታደርጉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡

#የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ ማድረጊያ ጊዜ 👇
ከነሐሴ 28/2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜን 05/2018 ዓ.ም

የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ የሚያደርጉበት ሊንክ 👇
https://student.ethernet.edu.et/

የሕክምና፣ የአካል ጉዳተኝነት፣ ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትያዎች እና ከስድስት ወር በታች ህጻን የሚያጠቡ እናቶች አስፈላጊውን ሕጋዊ ማስረጃ ማያያዝ ይኖርባችኋል ተብሏል።

30/08/2026

ማስታወቂያ
በፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለመማር ለተመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ።

ትምህርት ሚኒስቴር ለ2019 የትምህርት ዘመን ትምህርት በሚሰጥባቸው ነባርና አዲስ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች በ9ኛ እና 10ኛ ክፍል ተማሪዎችን አወዳድሮ ለመቀበል ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት ተመዝግባችሁ በመጠባበቅ ላይ ያላችሁና ለፈተና የተመረጣችሁ ተማሪዎች በተመዘገባችሁበት ሊንክ መለያ ኮዳችሁን ( Reference Number) በማስገባት ማየት የምትችሉ መሆኑ እንገልጻለን።

በተጨማሪም ለፈተና የተመረጣችሁ ተማሪዎች ፈተና የሚሰጠው በበየነ መረብ (online) ስለሆነ የሚቀርባችሁን የፈተና መስጫ ማዕከል በዛው ሊንክ በመግባት መምረጥ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን የሙከራ ፈተና እሮብ ነሃሴ 27/2018 ዓ.ም የሚሰጥ ሲሆን ዋና ፈተናው ነሃሴ 28/2018 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑ አውቃችሁ ዝግጅት እንድታደርጉ ለማሳሰብ እንወዳለን።

የተማሪዎች የዩኒቨርስቲ ቅያሪ በሚንስቴር መሰሪያ ቤቱ በኩል ብቻ መከናወን እንዳለበት ተገለጸ።
27/08/2026

የተማሪዎች የዩኒቨርስቲ ቅያሪ በሚንስቴር መሰሪያ ቤቱ በኩል ብቻ መከናወን እንዳለበት ተገለጸ።

26/08/2026
19/08/2026

Address

Dilla

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dilla University posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share