24/06/2026
ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ውጤት ጋር በተያያዘ ቅሬታ ያላቸው ተፈታኞች፣ እስከ ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ቅሬታቸውን ማቅረብ እንደሚችሉ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል።
ተፈታኞች በአካል መገኘት ሳያስፈልጋቸው ውጤት ባዩበት https://result.ethernet.edu.et/usernamepage ሊንክ በመግባት “Submit Complaint” የሚለውን አማራጭ በመጫን በኦንላይን ብቻ ማመልከት እንደሚችሉ የተገለጸ ሲሆን፣ የቅሬታ መቀበያ ጊዜው ከሰኔ 17 እስከ ሰኔ 23/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ እንደሚቆይ ተገልጿል።
ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ/ም