07/08/2026
ጋምቤላ ዩነቨርሲቲ ካውንስል የ2019 በጀት ዓመት የስራ ዕቅድን ገምግሞ አጸደቀ።
ህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት (ነሀሴ 1/2018 ዓ.ም)
የጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ካውንስል አባላት የ2019 በጀት ዓመት የሥራ ዕቅድን በጥልቀት በመገምገም እና አስፈላጊውን ማሻሻያ በማድረግ በሙሉ ድምፅ አጽድቋል።
የ2019 በጀት ዓመት የስራ ዕቅድ ግምገማውን የመሩት የጋምቤላ ዩነቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ድሪባ ኢትቻ በንግግራቸው እንደገለጹት የ2019 በጀት ዓመት የስራ ዕቅድ የ2018 በጀት ዓመት የቁልፍ አመላካቾች አፈፃፀም ግምገማን መነሻ በማድረግ መዘጋጀቱን ጠቅሰው የተዘጋጀው ዕቅድ ከየተኛውም ጊዜ በላይ የተሻለና የተቀናጀ መሆኑን አስረድተዋል።
ፕሬዝዳንቱ አክለውም ሰነዱ በ2019 በጀት ዓመቱን ሙሉ የምናከናውነው የጋራ እቅድ በመሆኑ የካውንስል አባላት በንቃት እንዲሳተፉና ገንቢ አስተያየት በመስጠት እንደዲያሻሽሉት ጋብዘዋል፡፡
የስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ሐጎስ ብርሃኔ የዩኒቨርሲቲውን ዓመታዊ ዕቅድ ለካውንስል አባላት ያቀረቡ ሲሆን ተቋማዊ መረጃዎች፣ የዩኒቨርሲቲው ተልዕኮ፣ ራዕይና እሴቶች፣ ያለፈው በጀት ዓመት የፕሮግራሞች አፈፃጸም ጥንካሬዎችና ማሻሻያ የሚሹ ጉዳዮች፣ የዕቅዱ መነሻ ሀሳቦች፤ ሰትራቴጂካዊ አቅጣዎችና የትኩረት መስኮች፣ ግቦች፣ ዓላማ፣ ዋና ዋና ተግባራት እና ማስፀሚያ ስልቶች እንዲሁም የድጋፍና ክተትል የግምገማ ስርዓት በዕቅዱ ተካተዋል፡፡
የዩኒቨርሲቲው የካውንስል አባላትም በቀረበው የ2019 በጀት ዓመት የስራ ዕቅድ ላይ ሰፊ ግምገማ ያካሄደ ሲሆን በተይም በ2019 በጀት ዓመት ድጂታላይዜሽንን ማስፋፋትና መጠቀም፣ የውስጥ ገቢ መሳደግ፣ አለም አቀፋዊነትን ማጠናከር፣ ችግር ፈቺ ጥናትና ምርምሮችን ማከሄድና አካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ማድረግ ላይ መስራቱ ይበልጥ ጠቀሜታ እንዳለው ተጠቅሷል።
በመጨረሻም የጋምቤላ ዩነቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ድሪባ ኢትቻ በክልሉ ያሉትን የተፈጥሮ ፀጋዎቸ በመጠቀም ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ መዘጋጀት፣ በዩኒቨርሲቲው ውሰጥ ምቹ የስራ አካባቢ መፍጠር፣ የተቋማዊ አቅም ግንባታና የገቢ ማስገኛ ስራዎች ላይ ሰፊ ስራዎችን መስራት፣ የተጀመሩ የግንባታ ፕሮጀክቶችን ማጠናቀቅ ሀገራችን ያለችበትን ሁኔታ በመረዳት የ2019 በጀት በልዩ ሁኔታ በትብብርና በትጋት በመስራት የተሻለ ለውጥ የምናስመዘግብበት ዓመት መሆን አለበት ሲሉ አሳስበው በእቅዱ ውስጥ ሳይካተቱ የተዘነጉ ጉዳዮች ካሉ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲካተቱ አስቀምጠዋል፡፡
Gambella University Council Evaluates and Approved 2019 fiscal year Annual Work Plan
Public and International Relations (August 7, 2026)
Members of the Gambella University Council have unanimously approved the 2019 Ethiopian Fiscal Year (EFY) work plan following a comprehensive evaluation and necessary refinements.
In his remarks, Dr. Diriba Etcha, President of Gambella University who led the evaluation of the 2019 fiscal year work plan, noted that the plan was prepared based on the performance evaluation of the 2018 fiscal year key performance indicators (KPIs). He explained that the drafted plan is more comprehensive and well-integrated than ever before.
The President further added that since the document serves as a shared plan to guide all institutional ex*****on throughout the 2019 fiscal year, council members should actively participate and enrich it by providing constructive feedback.
Dr. Hagos Berhane, Executive Director for Strategic Affairs, presented the University's annual plan to the council members. The plan incorporates institutional profile, the University's mission, vision, and core values, program performance strengths and areas requiring improvement from the previous fiscal year, Initial Concepts of the plan, strategic directions and priority focus areas, goals, objectives, main activities, and ex*****on strategies, as well as support, monitoring, and evaluation systems.
Following the presentation, council members engaged in extensive deliberations, highlighting several critical strategic priorities for the 2019 fiscal year.
These priorities focused on expanding digital infrastructure and adoption, boosting internal revenue generation, and enhancing the institution's internationalization efforts. Additionally, the council emphasized the importance of conducting problem-solving research that directly empowers and benefits the local community.
In his concluding remarks, Dr. Diriba Etcha provided several key directives to guide the University's upcoming efforts. He emphasized leveraging the region's natural resources to benefit surrounding communities, creating a conducive working environment across all University campuses, and aggressively executing institutional capacity-building initiatives and revenue-generating projects completing ongoing construction projects.
Finally, he called for exceptional dedication and collaboration in light of the national context, instructing the council to swiftly integrate any remaining omitted items into the final plan.