ታችአርማጭሆ ወረዳ ትም/ት ጽ/ቤት 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ማዕከል

  • Home
  • Ethiopia
  • Gondar
  • ታችአርማጭሆ ወረዳ ትም/ት ጽ/ቤት 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ማዕከል

ታችአርማጭሆ ወረዳ ትም/ት ጽ/ቤት  2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ማዕከል Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ታችአርማጭሆ ወረዳ ትም/ት ጽ/ቤት 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ማዕከል, College & University, Amhara region, Gondar.

 # #አቶ ክንዱ ዘውዱየማዕከላዊ ጎንደር ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ትምህርት መምሪያ፣ ከጠቅላላ ሠራተኞቹ ጋር በ2018 ዓ.ም በተገኘው የዕቅድ አፈጻጸም ውጤት እና ...
19/08/2026

# #አቶ ክንዱ ዘውዱ
የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ትምህርት መምሪያ፣ ከጠቅላላ ሠራተኞቹ ጋር በ2018 ዓ.ም በተገኘው የዕቅድ አፈጻጸም ውጤት እና ለቀጣይ ዓመት ባቀዳቸው የሥራ አቅጣጫዎች ዙሪያ ገንቢ ውይይት አድርጓል።

በዚህ የግምገማ ሂደት፣ መምሪያው ባለፈው ዓመት ያገኘው ውጤት ትልቅ ፋይዳ ያለው መሆኑ ተገልጿል ። አቶ ክንዱ እንዳስታወሱት፣ በተከናወኑ ሥራዎች ላይ የተሰጠው እውቅና ለሠራተኞቹ ማበረታቻ ሲሆን፣ ይሁን እንጂ የተገኘውን ስኬት ለማስቀጠልና ደረጃውን ለማሻሻል ቀጣይ ተግባራትን በአግባቡ መፈጸም እዳ መሆኑን አሳስበዋል።

ከሁሉ በላይ ግን፣ የትምህርት አገልግሎታችን ዋና ተጠቃሚ ማኅበረሰባችን ተጨባጭ ጥቅም እንዲያገኝ ማድረግ የሁላችንም ዋነኛ ሃላፊነት መሆኑን አጥብቀው ገልጸዋል።

በመቀጠልም፣ የመምሪያው ምክትል ኃላፊ አቶ ነጋ ብርሀኑ ለሠራተኞቹ እንኳን ለተገኘው ስኬት ደስ አላችሁ በማለት እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል። በተጨማሪም፣ የ2019 ዓ.ም የተማሪ ምዝገባን በአግባቡ በማካሄድ እና የትምህርት ሥራችንን ውጤታማነት በማረጋገጥ ያለፈውን ስኬት መድገም እንደሚገባ አሳስበዋል።

 # #ለ2019 የትምህርት ዘመን ከ870 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ለመመዝገብ የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ትምህርት መምሪያ ዝግጅት አጠናቀቀ # #የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ  # ...
19/08/2026

# #ለ2019 የትምህርት ዘመን ከ870 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ለመመዝገብ የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ትምህርት መምሪያ ዝግጅት አጠናቀቀ

# #የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ # #አቶ ክንዱ ዘውዱ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳሳወቁት፤ ዞኑ ለ2019 የትምህርት ዘመን ከቅድመ-አንደኛ እስከ 12ኛ ክፍል እንዲሁም በልዩ ልዩ የትምህርት ፕሮግራሞች ከ870 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ለመመዝገብ የሚያስፈልጉ ቅድመ ዝግጅቶችን አጠናቋል።

# #በአማራ ክልል ከተያዘው 7 ሚሊዮን ተማሪዎች ምዝገባ እቅድ ውስጥ ዞኑ ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛል። ለዚህም ከህብረተሰብ ተወካዮች፣ ከወላጅ-መምህር-ተማሪ ህብረት (ወተመ)፣ ከሃይማኖት አባቶች እና ከሀገር ሽማግሌዎች ጋር ሰፊ ውይይት መደረጉንም አመልክተዋል።

# #የምዝገባ ስራው ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ይጀመራል። ከዚህ ቀደም በሁሉም 15 ወረዳዎች በተመረጡ ትምህርት ቤቶች የሙከራ (ፓይለት) ምዝገባ ይካሄዳል። የትምህርት መዋቅር በሌላቸው 4 የከተማ አስተዳደሮች (አምባ ጊዮርጊስ፣ አያከል፣ ቆላድባ እና ሻውራ) ስራው እንዳይስተጓጎል ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ቅንጅት ተደርጓል።

# #በ2017 የትምህርት ዘመን ከ600 በላይ ትምህርት ቤቶች ተዘግተው ከ600 ሺህ በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጭ የነበሩ ቢሆንም፣ በማህበረሰቡ ንቁ ተሳትፎ እና በትምህርት ለትውልድ ኢኒሼቲቭ አማካኝነት # #በ2018 አበረታች ውጤት መመዝገቡ ተጠቅሷል። በተለይም በ2018 የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና 86%፣ የ8ኛ ክፍል ደግሞ 83% ተማሪዎች ማለፋቸው ተገልጿል።

# #ለ2019 የትምህርት ዘመን የትምህርት ቤቶችን ገጽታና ግብዓት ለማሻሻል፦

· በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ438 በላይ አዳዲስ የመማሪያ ክፍሎች ተገንብተዋል፤
· የትምህርት ቤት አጥር፣ ጥቁር ሰሌዳዎች፣ ወንበሮች፣ በሮች እና መስኮቶች ጥገና ተካሂዷል፤
· ለአካል ጉዳተኛ ተማሪዎችና መምህራን የተቋማት ራምፕ (መድረሻ) ዝግጅትን ጨምሮ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል።

# #ከ50 ሺህ በላይ ጎልማሶችን ለማስተማር የታቀደ ሲሆን፣ ከማንበብና መጻፍ ባሻገር በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች አጫጭር የክህሎት ስልጠናዎች (በብረት፣ እንጨት፣ ባልትና እና ዶሮ እርባታ) እንዲያገኙ ይደረጋል።

# #ከ370 በላይ የትምህርት ቤት አመራሮች እና ከ2,100 በላይ መምህራን በትምህርት ጥራትና አመራር ዙሪያ ስልጠና ወስደዋል። ከ5ኛ ክፍል በላይ ያሉ ከ10 ሺህ በላይ ተማሪዎች በክረምት የማካካሻ ትምህርት ተከታትለዋል።

ኃላፊው ትምህርት ሙሉ በሙሉ ሴኩላር ሆኖ በማህበረሰብ ባለቤትነት መመራት እንዳለበት አሳስበው፤ በ2019 የትምህርት ዘመን # #አንድም ተማሪ ከትምህርት ገበታ ውጭ መሆን እንደሌለበት በማጉላት ህብረተሰቡ እና ሚዲያው በምዝገባ ስራው የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

 # #አባይ ህትመት እና ወረቀት ፓኬጅንግ ፋብሪካ ለ60 ሺህ ደብተሮች ድጋፍ አደረገ !!ባህር ዳር፡- የ2019 የትምህርት ዘመን “አንድ ደርዘን ደብተር ለአንድ ተማሪ” የተማሪዎች የመማሪያ ...
19/08/2026

# #አባይ ህትመት እና ወረቀት ፓኬጅንግ ፋብሪካ ለ60 ሺህ ደብተሮች ድጋፍ አደረገ !!

ባህር ዳር፡- የ2019 የትምህርት ዘመን “አንድ ደርዘን ደብተር ለአንድ ተማሪ” የተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ማሰባሰቢያ ባዛር በባህር ዳር ከተማ ጊዮርጊስ አደባባይ ተከፍቷል።

በባዛሩ ላይ የተገኘው የአባይ ህትመት እና ወረቀት ፓኬጅንግ ፋብሪካ ለተማሪዎች ድጋፍ ሲያደርግ የቆየ ሲሆን፣ በዚህም ጊዜ 60 ሺህ ደብተሮችን ለትምህርት ቁሳቁስ ማሰባሰቢያ ባዛሩ አበርክቷል።

ድጋፉን ያስረከቡት የአባይ ህትመት እና ወረቀት ፓኬጅንግ ፋብሪካ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ነጋ ይሁኔ እንደገለጹት፣ ፋብሪካው ተማሪዎች በትምህርት ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ከትምህርት ገበታ ውጭ እንዳይሆኑ ለማስቻል በተከታታይ አመታት ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን አስረድተዋል። በቀጣይም ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አመላክተዋል።

የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ማሰባሰቢያ ባዛሩ ከዛሬ ረቡዕ ነሐሴ 13 ጀምሮ እስከ ነሐሴ 15/2018 ዓ.ም ለተከታታይ ሶስት ቀናት የሚቀጥል ይሆናል።


✨ ሰበር የድጋፍ ዜና ከታላቋ ብሪታንያ 🇬🇧🕺🕺✨ # #ተማሪዎቻችን በቁሳቁስ እጥረት ከትምህርት ገበታቸው እንዳይቀሩ የቀረበውን ጥሪ በመቀበል፣ በአርማጭሆና አካባቢው በሚሰሩ የበጎ አድራጎት ስ...
19/08/2026

✨ ሰበር የድጋፍ ዜና ከታላቋ ብሪታንያ 🇬🇧🕺🕺✨
# #ተማሪዎቻችን በቁሳቁስ እጥረት ከትምህርት ገበታቸው እንዳይቀሩ የቀረበውን ጥሪ በመቀበል፣ በአርማጭሆና አካባቢው በሚሰሩ የበጎ አድራጎት ስራዎች ሁልጊዜም ከጎናችን የምትቆመው፣ በቅን አስተሳሰቧና ለሰው ልጅ ባላት ታላቅ ክብር የምናውቃት፣ # #ለአርማጭሆ ልማትና እድገት የምትቆረቆረው ሳቂታዋ እህታችን ማናሌ አዳነ ከእንግሊዝ🇬🇧 15,000 (አስራ አምስት ሺህ) ብር ድጋፍ በማድረግ ለ ህፃናትን ተስፋ አብሪ ኮከብ ሆናለች ።

ርቀት ሳይገድባት ለወገኖቿ ደራሽ በመሆን ላሳየችው አርአያነት ያለው እህትነትና ስላበረከተችው ድንቅ አስተዋጽኦ ከልብ እናመሰግናለን! ፈጣሪ ይስጥልን! 🙏✨❤️

ለተጨማሪ መረጃዎች በሚከተሉት ሊንኮች እየገባችሁ Share፣ Comment እና Like አድርጉ።

=> Edlamu Alemie
=> Lij Solomon Abye
=> Getachew Abera
=> Belay Wondifraw Asresa

አንዳንዴ ግርምት  የሚፈጥሩብን በጎ-ሰዎችን  ምንብለን እንደምገልጻቸው ይከብደናል  !! በሰሜን ቤጌ-ምድር  # #ለእህታችን ትግስት (ቲጂ የባህርዳራ) ከልብ የመነጨ ምስጋና! ዛሬ በወንድማች...
18/08/2026

አንዳንዴ ግርምት የሚፈጥሩብን በጎ-ሰዎችን ምንብለን እንደምገልጻቸው ይከብደናል !! በሰሜን ቤጌ-ምድር
# #ለእህታችን ትግስት (ቲጂ የባህርዳራ) ከልብ የመነጨ ምስጋና! ዛሬ በወንድማችን # #ገብናናው የቲክቶክ ቀጥታ ስርጭት ላይ በትውልድ ግንባታ ዙሪያ ያየነው ልዩ ልግስና ልባችንን አነካ።

በስደት አገር ብትኖርም፣ ልቧ ግን ሁልጊዜ ከኢትዮጵያ ልጆች ጋር የሆነችው፣ የበጎ አድራጎት አምባሳደር እህታችን ትግስት፣ ተማሪዎቻችን በቁሳቁስ እጥረት ከትምህርታቸው እንዳይቀሩ የቀረበውን ጥሪ በአዎንታዊ ልብ ተቀብላ አስደናቂ ድጋፍ አድርጋለች።

ድጋፏም በዚህ መልኩ ነው፦
🔹 በራሷ ስም – 10,000 ብር
🔹 በወንድማችን ገብናናው ስም – 2,500 ብር
🔹 በሁላገር ስም – 2,500 ብር
🔹 በባለቤቷ ስም – 5,000 ብር

ጠቅላላ፡ 20,000 (ሃያ ሺህ) ብር!

ከዚህም በላይ ራሷ በመደገፍ ብቻ ሳትወሰን፣ ሌሎችንም በማስተባበር ለብዙ በጎ ስራዎች መሳካት ትልቅ አሻራ ያላትን ውድ እህታችንን፣

በቅንነትሽ፣ በርህራሄሽና በትውልድ ላይ ያለሽ ፍቅር እጅግ እናመሰግናለን!
ፈጣሪ እድሜና ጤና ሰጥቶሽ፣ በረከቱንም ያብዛልሽ! መልካም ስራሽ ለሁላችንም መነሳሻ ይሁን!

ለተጨማሪ መረጃ ከታች ባሉት ሊንኮች በመግባት Share፣ Comment እና Like በማድረግ ይህን መልካም ተግባር እናስፋፋ!
👉 Edlamu Alemie
👉 Lij Solomon Abye
👉 Getachew Abera
👉 Belay Wondifraw Asresa
#ኢትዮጵያ

 # #ለምስራቅ ደምቢያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሐብቴ ብርሌ የዋንጫ ሽልማት ተበረከተ !!በምስራቅ ደምቢያ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት የ2018ዓ.ም በጀት ዓመት ማጠቃለያ ፣ በወረዳው የትምህር...
18/08/2026

# #ለምስራቅ ደምቢያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሐብቴ ብርሌ የዋንጫ ሽልማት ተበረከተ !!
በምስራቅ ደምቢያ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት የ2018ዓ.ም በጀት ዓመት ማጠቃለያ ፣ በወረዳው የትምህርት ዘርፍ ልዩ አስተዋጽዖ ላበረከቱት ለወረዳው ዋና አስተዳዳሪ # #አቶ ሐብቴ ብርሌ የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

# #አቶ ሐብቴ ብርሌ በስራ ዘመናቸው ለትምህርት ጥራት ማሻሻል፣ ለመምህራን ሙያዊ እድገት እንዲሁም ለተማሪዎች የተሻለ የትምህርት አጋጣሚ በመፍጠር ያደረጉት ጥረት እጅግ አመስጋኝ መሆኑ ተገልጿል። ይህ ሽልማት ለልማት ስራዎቻቸው ያለው እውቅና እንደሆነ የትምህርት ጽ/ቤቱ አስረድቷል ።

በዚህ የእውቅና ሽልማት ላይ የወረዳው የትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊዎች እና ሌሎች የዘርፉ ባለሙያዎች የተገኙ ሲሆን፣ ሽልማቱን ሲቀበሉ # #አቶ ሐብቴ ብርሌ ለሁሉም አጋሮች ምስጋና አቅርበው ለወደፊትም ትምህርቱን የበለጠ ለማሳደግ ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል ።

ምስራቅ ደምቢያ መንግስት ኮሙኒኬሽን
ነሐሴ 12/2018 ዓ.ም

18/08/2026
 # #በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ታች አርማጭሆ ወረዳ ትምህርት ጽሕፈት ቤት "ከግምገማ ወደ ተግባር፤ ከተግባር ወደ ላቀ ውጤት!" በሚል መሪ ቃል የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ እ...
18/08/2026

# #በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ታች አርማጭሆ ወረዳ ትምህርት ጽሕፈት ቤት "ከግምገማ ወደ ተግባር፤ ከተግባር ወደ ላቀ ውጤት!" በሚል መሪ ቃል የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 ዓ.ም ዕቅድ ትውውቅ የንቅናቄ መድረክ አካሄደ።

# #በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ # #አቶ እንዳላማው ዘውዱ፤ ለአገር ሁለንተናዊ እድገትና ልማት ቁልፍ በሆነው የትምህርት ዘርፍ የሚታዩ ክፍተቶችን በጥራት ለመሸፈንና ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣት የምሁራን ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። "ውጤታማና ቀልጣፋ የአገልግሎት አሰጣጥ ለሀገር ግንባታ ሙህራን የላቀ ሚና አላቸው" በማለት አሳስበዋል።

አክለውም፣ የመሠረተ ልማት አቅርቦታቸው የተሟላ ትምህርት ቤቶች በእውቀት የበለጸገ ትውልድ በመቅረጽ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳላቸው ጠቁመው፤ ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደትን በማስቀጠል የመጪውን ትውልድ ብሩህ ተስፋ ዕውን ማድረግ እንደሚገባ ገልጸዋል። በመሆኑም ትምህርት ቤቶችን ለማሻሻልና የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን እንቅስቃሴ ሁሉም አካል በሙሉ ልብ ሊደግፈው እንደሚገባ አሳስበዋል።

# #የወረዳው ትምህርት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ # #አቶ አንጋው መጣለም በበኩላቸው፤ በ2018 በጀት ዓመት በመማር ማስተማር ሥራዎች ላይ የታዩ ጥንካሬዎችንና ድክመቶችን በዝርዝር መለየት እንደሚገባ ገልጸው፤ የታዩ ድክመቶችን ፈጥኖ በማስተካከል፣ ጥንካሬዎችን በማጠናከርና በማስፋት መሥራት እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።

ኃላፊው አክለውም፤ በ2019 ዓ.ም የስራ ዘመን ሥራን በጥብቅ ዲሲፕሊን በመምራት፣ መልካም ተሞክሮዎችን በማስፋት፣ የአመለካከትና የሥነ-ምግባር ጉድለቶችን ታግሎ በማሸነፍ ሥራ መሥራት እንደሚገባ ገልጸዋል። በሌላ በኩልም የአገልግሎት አሰጣጡን በማዘመንና የመማር ማስተማር ሂደቱን ዲጂታላይዝ በማድረግ የተጣለባቸውን ሀገራዊ ኃላፊነት በአግባቡ መወጣት እንደሚገባቸው አሳስበዋል።

# #በመጨረሻም፤ በወረዳው ትምህርት ጽሕፈት ቤት የዕቅድ ዝግጅት ቡድን መሪ ባለሙያ # #በአቶ ዛየደ ፈንታሁን አቅራቢነት የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2019 ዓ.ም ዕቅድ የመወያያ ሰነድ ለተሳታፊዎች ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል።

እንኳን አደረሳችሁ ለመላው ህዝበ ክርስቲያን ኢትዮጵያውያን የቡሄ (ደብረ ታቦር) በዓል !! "መጣና በዓመቱ... ኧረ እንደምን ሰነበቱ!" የሚለው የታዳጊዎች ጭፈራና ዜማ ዛሬ በሁሉም የኢትዮጵ...
18/08/2026

እንኳን አደረሳችሁ ለመላው ህዝበ ክርስቲያን ኢትዮጵያውያን የቡሄ (ደብረ ታቦር) በዓል !!

"መጣና በዓመቱ... ኧረ እንደምን ሰነበቱ!" የሚለው የታዳጊዎች ጭፈራና ዜማ ዛሬ በሁሉም የኢትዮጵያ ማዕዘናት ይሰማል፤ ምክንያቱም የክረምቱ ቅዝቃዜና ጨለማ ተሸንፎ የፀሐይ ብርሃን፣ የልምላሜና የተስፋ ወቅት መምጣቱን የምናበስርበት ይህ ታላቅ በዓል ነው።

ቡሄ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች የኢየሱስ ክርስቶስ መለኮታዊ ብርሃን በደብረ ታቦር ተራራ ላይ መገለጡን የሚያስታውስ መንፈሳዊ በዓል ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያዊነታችንን መለያ የሆኑትን ማካፈልን፣ መተሳሰብን፣ እንግዳ ተቀባይነትንና አንድነትን በሚገለጽ መልኩ የሚከበር ሕዝባዊ ሃብታችን ነው።

ከደብረ ታቦር እስከ ሰሜን ወሎ፣ ከጎጃም እስከ ሸዋ፣ ከወሎ እስከ ሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች ድረስ በተለያዩ ቋንቋዎችና ባህሎች ቢከበርም፣ ዋናው መልእክቱ ግን አንድ ነው — ብርሃን ድል አድራጊ ነው፣ አንድነታችን ጥንካሬያችን ነው።

በዚህ በዓል ልጆች በሆያ ሆዬ ዜማቸው በየደጁ ሲያበሩ፣ እናቶች ሙልሙልን እያደሉ፣ አባቶች ደግሞ በምርቃት እያበረከቱ የሚያሳዩት የመተባበር እና የመደጋገፍ ባህላችን ትውልድን የሚያስተሳስር ኃይለኛ መሰረት ነው።

ይህ በዓል መንፈሳዊ ጥልቀቱን ጠብቆ ማህበራዊ ትስስራችንን ከማጠናከር ባለፈ፣ የኢትዮጵያን የበጎ ገጽታ ለዓለም በማስተዋወቅ የቱሪዝም ኢኮኖሚያችንንም ከፍ የሚያደርግ ድንቅ ብሔራዊ ፀጋችን ነው።

ከዚህም በላይ፣ ቡሄ በጨለማ ውስጥ ብርሃንን፣ በተስፋ መቁረጥ ውስጥ ተስፋን፣ በመለያየት ውስጥ አንድነትን እንድናይ የሚያስተምረን የሕይወታችን ትምህርት ነው።

ስለዚህ፣ ለሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች፣ እንዲሁም ይህን ባህላዊ ሃብታችንን በአክብሮት ለሚቀበሉ ሁሉ፣ እንኳን አደረሳችሁ!

ብርሃናችን ይብራራል፣ አንድነታችን ይጠነክራል፣ ኢትዮጵያችን ትደግ።

🌟 መልካም የቡሄ በዓል ይሁንላችሁ! 🔥🙏

 #ደቡብ  #ወሎ  #ዞን  #ትምህርት  #መምሪያ  #በክልል  #ደረጃ  #1ኛ  #ደረጃ  #በመሆን  #የዋንጫና  #የእውቅና  #ሽልማት  #ተበረከተለትየአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2018 የት...
18/08/2026

#ደቡብ #ወሎ #ዞን #ትምህርት #መምሪያ #በክልል #ደረጃ #1ኛ #ደረጃ #በመሆን #የዋንጫና #የእውቅና #ሽልማት #ተበረከተለት

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2018 የትምህርት ዘመን የእቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 ዓ.ም የእቅድ ትውውቅ መድረኩን ባጠናቀቀበት መድረክ፣ በዞን ደረጃ በሁሉም የትምህርት ዘርፍ ዘርፈ-ብዙ የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገበው ለደቡብ ወሎ ዞን ትምህርት መምሪያ የ1ኛ ደረጃ እውቅና፣ የኮምፒውተርና የፕሪንተር ሽልማት አበረከተ፡፡

በክልሉ ትምህርት ቢሮ ግምገማ መሰረት በ2018 የትምህርት ዘመን በዞኑ የተመዘገቡት ስኬቶች የትምህርት አመራሩና የህብረተሰቡ የጋራ ጥረት ውጤት መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን፣ መምሪያው በተለይም፡-

በ6ኛ እና በ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተናዎች የተሻለና አበረታች ውጤት በማስመዝገብ፣ ቅድመ-አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በማስፋፋትና ራስን እንዲችሉ በማድረግ፣ የተማሪዎች የምገባ ፕሮግራሞችን በማጠናከር፣ በ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የነበረውን የኮምፒውተር እጥረት ለመፍታት በተደረጉ ጥረቶች፣ እንዲሁም የትምህርት ቤት መሰረተ-ልማቶችን በማስፋፋት ረገድ ባሳየው የላቀ እንቅስቃሴ ከክልሉ ዞኖች 1ኛ ደረጃ በመያዝ አሸናፊ ሆኗል፡፡

ይህንን ታላቅ ውጤት ያስመዘገበው የደቡብ ወሎ ዞን ትምህርት መምሪያ የተዘጋጀለትን የኮምፒውተር፣ የፕሪንተርና የእውቅና ሰርተፍኬት ሽልማት ከክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥላሁን ወርቅነህ እጅ ተረክቧል፡፡

መምሪያው ያስመዘገበውን ይህንን የላቀ አፈጻጸም ይበልጥ ለማስቀጠልና በ2019 የትምህርት ዘመን ታቅደው የተያዙትን ተግባራት ለማስፈጸም፣ ነሐሴ 18/2018 ዓ.ም የሚጀመረውን የተማሪዎች ምዝገባ ጨምሮ ሁሉንም አዲስና ነባር ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታ ለማምጣት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ ታውቋል፡፡

Address

Amhara Region
Gondar
A

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ታችአርማጭሆ ወረዳ ትም/ት ጽ/ቤት 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ማዕከል posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share