University of Gondar

University of Gondar The University of Gondar is an esteemed institution of higher learning in Ethiopia, founded in 1954.
(3)

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሳሳካዋ አፍሪካ አሶሴሽን (Sasakawa Africa Association) ከተባለ ዓለም አቀፍ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር የጋራ መግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ፡፡───የመግባቢያ ሰ...
27/08/2026

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሳሳካዋ አፍሪካ አሶሴሽን (Sasakawa Africa Association) ከተባለ ዓለም አቀፍ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር የጋራ መግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ፡፡

───

የመግባቢያ ሰነዱን የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር የቻለ ከበደ እና ዶ/ር ኤርምያስ አባተ የሳሳካዋ አፍሪካ አሶሴሽን (Sasakawa Africa Association) ምክትል ዋና ዳይሬክተር ጋራ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ህንፃ ዛሬ ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም. ተፈራርመዋል፡፡

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር የቻለ ከበደ በጋራ መግባቢያ ሰነድ ፊርማ ስነ-ስርዓት ላይ እንደገለፁት የሳሳካዋ አፍሪካ አሶሴሽን ከዚህ ቀደም በርካታ ተግባራትን ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ጋር በጋራ ሲያከናውን የቆዬ ቢሆንም ዛሬ ግን የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ወደ ራስ ገዝነት በምናደርገው ጉዞ በአቅም ግንባታ እና በተለያዩ የልማት መስኮች በአጋርነት ትውልድን የሚጠቅምና በግብርናው ዘርፍ ውጤታማ የሚያደርግ ተግባራትን በጋራ እናከናውናለን ብለን ተስፋ እናደርጋለን ብለዋል፡፡

የሳሳካዋ አፍሪካ አሶሴሽን (Sasakawa Africa Association) ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ኤርምያስ አባተ በበኩላቸው ሳሳካዋ አፍሪካ በኢትዮጵያ የግብርና ኤክስቴንሽን፣ የምግብ ዋስትና እና ዘላቂ የግብርና ስልጠናዎችን ሲሰጥ የቆየ ዓለም አቀፍ ግብረ ሰናይ ድርጅት መሆኑን ገልፀዋል፡: የግብርናው ዘርፍ የማይተካ ሚና ያለው ዘርፍ መሆኑን እና ዛሬ የምንሰራው ስራ ሁሉ ከተፈጥሮ ሀብት ጋር የሚጋጭና አጥፊ እንዳይሆን መጠንቀቅ ይገባናል ብለዋል፡፡ ሳሳካዋ ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ጋር በጋራ በመስራት የአርሶ አደራችን ህይወት ለመለወጥ የአቅማችን እገዛ እናደርጋለን ሲሉ ዳይሬክተሩ አስረድተዋል፡፡

በግብርና ሚኒስቴር የእርሻና ሆርቲካልቸር ኤክስቴንሽን መሪ ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ የኔነሽ ኢጉ እንደገለጹት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ እጅግ ትልቅ ተቋም መሆኑን ጠቅሰው የዛሬው የመግባቢያ ሰነድም ከዚህ በፊት ሲሰሩ ከነበሩት ተግባራት በተሻለና በላቀ ደረጃ ውጤታማ ለማድረግ እንደ ግብርና ሚኒስቴር የሚጠበቅብንን ድጋፍ እንደምናደርግ ቃል እንገባለን ብለዋል፡፡

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር ካሳሁን ተገኘ በበኩላቸው ሰነዱ ዩኒቨርሲቲያችንና የሳሳካዋ አፍሪካ አሶሴሽን ሀገራችን ለምትጠብቀው የግብርና እድገት ወሳኝ ሚና እንዲጫወቱና የኤክስቴንሽን ሰራተኞችን ትምህርት ከፍ በማድረግ ግብርናውን እንዲደግፉ የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡

የግብርና እና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ ዲን ዶ/ር ዳንኤል ታደሰ በሁለቱ ተቋማት የሚፈጠረው ትብብር በግብርና ልማት፣በእውቀት ሽግግር እና በአቅም ግንባታ ዘርፍ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚያስገኝ አስረድተዋል፡፡

በጋራ መግባቢያ ሰነዱ ፊርማ ላይ ዲኖች፣ ዳይሬክተሮች፣ ተመራማሪዎች እና መምህራን ተገኝተዋል፡፡

───

ለልህቀት እንተጋለን!
የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ
ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም

ስኬሊንግን በስርዓተ ትምህርት ውስጥ ለማካተት ያለመ የሁለት ቀናት ወርክሾፕ ተካሄደ******************************የግብርና ዘርፍ ትምህርት  ጥራትን ለማሳደግ እንዲሁም ይዘቶች...
27/08/2026

ስኬሊንግን በስርዓተ ትምህርት ውስጥ ለማካተት ያለመ የሁለት ቀናት ወርክሾፕ ተካሄደ
******************************
የግብርና ዘርፍ ትምህርት ጥራትን ለማሳደግ እንዲሁም ይዘቶችን በስፋት ተዳራሽ ለማድረግ የሚያስችሉ የማስተማሪያ ሞጁሎችን በግብርና ኮሌጅ ሚድ ኬርየር ፕሮግራም ስርዓተ ትምህርት ለማካተት ያለመ የሁለት ቀናት አውደ ጥናት ነሀሴ 19 እና 20 ቀን 2018 ዓ.ም ተካሄደ። ወርክሾፑን የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከአለም አቀፍ የውሃ ምርምር ተቋም ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ነው።

"Co-creation and Validation Workshop for Scaling Science Learning Modules" በተሰኘው በዚህ የምክክር መድረክ ከአማራ ክልል ግብርና ቢሮ፣ ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ የግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ እና የእንስሳት ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ፣ ከባህርዳር ዩኒቨርሲቲ፣ ከደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ፣ ከወረታ እና ከኮምቦልቻ ግብርና ኮሌጅ እንዲሁም ከጎንደር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተውጣጡ መምህራን፣ ተመራማሪዎችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

የመድረኩን መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ ዲን ዶክተር ዳንኤል ታደሰ ሲሆኑ፣ በመቀጠልም ዶክተር ዳንኤል ንጉሴ የስኬሊንግ ይዘቶችን በካሪኩለም ደረጃ የመቅረፅ ዋና ዋና ዓላማዎችና የሚጠበቁ ውጤቶችን ለተሳታፊዎች ገልጸዋል።

በሀገራችን የከፍተኛ ትምህርት እንዲሁም የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና (TVET) ዘርፍ ውስጥ የምርምር እና የሳይንሳዊ ውጤቶችን በማስፋት (scaling) ለህብረተሰቡ ፈጣን እና ዘላቂ ጥቅም ማድረስ የሚያስችሉ ጥራት ያላቸውን የመማሪያ ሞጁሎች በጋራ ማዘጋጀት ያለውን ጠቀሜታ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ምክትል ፕሬዚዳንት ልዩ ረዳት ዶ/ር መንግስቱ ሙሉ ገልፀዋል፡፡

በተጨማሪም በኢትዮጵያ ያለውን የዩኒቨርሲቲ እና የቴክኒክና ሙያ (TVET) ትስስር እንዲሁም ስኬሊንግን በካሪኩለም የመቅረጽ ሁኔታን የተመለከተ ዳሰሳ በሚስ ኒና ኖሃይ የቀረበ ሲሆን፣ ዶክተር ዴኒስ ቾሩማ ደግሞ የትምህርት ሞጁሎቹን ጥራትና የስኬሊንግ ውጤታማነት ለመለካት የሚያስችል የምዘና ማዕቀፍ (Assessment Framework) አቀራረብ ላይ ገለጻ አድርገዋል።

በመርሃ ግብሩ ለእያንዳንዱ ሞጁል አጭር ማብራሪያ ከተሰጠ በኋላ ተሳታፊዎች በትንንሽ ቡድኖች ተከፋፍለው የስኬሊንግ ይዘቶች በሚካተቱባቸው የሞጁል ክፍሎች (Units) ላይ የጋራ ግምገማና አስተያየት ሰጥተዋል። የስኬሊንግ ጽንሰ-ሀሳብን በካሪኩለም ውስጥ አዋህዶ የትምህርት ይዘቶችን የበለጠ ማጠናከር የሚቻልባቸው እድሎችም ተለይተዋል።
ወደፊትም የሞጁል ረቂቆችን የማጠናቀቅ እና በቀጣይ በሙከራ ደረጃ (Piloting) ተግባራዊ የማድረግ ስራዎችና የኃላፊነት ክፍፍሎች ላይ ውሳኔ ተተላልፏል።

በወርክሾፑ የተዘጋጁት አጋዥ ሞጁሎች የስኬሊንግ ጽንሰ-ሀሳብን መሠረት በማድረግ ከተግባራዊው የግብርናና የእንስሳት ህክምና ሳይንስ ጋር ተጣጥመው የተቀረፁ በመሆናቸው፣ ለተማሪዎችና ሰልጣኞች ጥራት ያለው እውቀት ለማስተላለፍ ከፍተኛ ሚና እንደሚኖራቸው ታምኖበት አውደ ጥናቱ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።
*******************
ለልህቀት እንተጋለን!
የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ
ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም

26/08/2026
26/08/2026
እንኳን ደስ አለን!የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሞዴል 2ኛ ደረጃ  ትምህርት ቤት እና የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ የማለፊያ ነጥብ አስመዘገቡ*************...
26/08/2026

እንኳን ደስ አለን!

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ የማለፊያ ነጥብ አስመዘገቡ
***********************
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና የተፈተኑት ሁሉም ተማሪዎቻቸው የማለፊያ ነጥብ በማስመዝገብ አንጸባራቂ ድል አስመዝግበዋል።

ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ረድኤት ሳሙኤል 574.4 ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ እንዲሁም ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ትምህርት ቤት ደግሞ ተማሪ ናትናኤል ሙላት 570.16 ውጤት በማስመዝገብ አስደናቂ ስኬት ተጎናፅፈዋል።

ለዚህ ታሪካዊ ውጤት መመዝገብ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ የትምህርት ቤቶቹ የማኔጅመንት አባላት፣ የመምህራንና የወላጆች ያልተቋረጠ ድጋፍ እንዲሁም የተማሪዎቹ ጥረት ከፍተኛው ድርሻ አላቸው።

ተማሪዎቻችን ነገ ሀገራቸውንና ህዝባቸውን በታማኝነትና በብቃት የሚያገለግሉ፣ ለታላቅ ቁምነገር የሚበቁ ዜጎች እንዲሆኑልን መልካም ምኞታችንን እንገልጻለን።
*********************
ለልህቀት እንተጋለን!
የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ
ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም

በጎንደር ዩኒቨርሲቲ በአፄ ቴዎድሮስ ግቢ የሚገኘው ትልቁ ፓርክ በዶ/ር አሥራት አፀደወይን ስም ተሰየመ:: ******************************በሀገር አቀፍ ደረጃ እንዲሁም ለተቋሙ...
26/08/2026

በጎንደር ዩኒቨርሲቲ በአፄ ቴዎድሮስ ግቢ የሚገኘው ትልቁ ፓርክ በዶ/ር አሥራት አፀደወይን ስም ተሰየመ::

******************************

በሀገር አቀፍ ደረጃ እንዲሁም ለተቋሙ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ የሀገር ባለውለታዎችና ዩኒቨርሲቲውን በኃላፊነት መርተው ለዚህ ደረጃ ላበቁ መሪዎች በስማቸው ህንፃዎችንና መሰረተ-ልማቶችን ስያሜ መስጠት በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የተለመደ የምስጋና ባህል ነው። ይህንኑ አሰራር በመከተል፣ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ በአፄ ቴዎድሮስ ግቢ የሚገኘው ትልቁ ፓርክ ዛሬ ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ.ም በዶክተር አሥራት አፀደወይን ስም ተሰይሟል። ስያሜው ዶ/ር አሥራት አፀደወይን በተቋሙ ምቹ የመማር ማስተማር ሁኔታን ለመፍጠርና ግቢው እጅግ ሳቢ የምርምር ማዕከል እንዲሆን ላደረጉት ሁለንተናዊ አስተዋፅኦና ላሳዩት የላቀ አመራር እውቅና ለመስጠት የተደረገ ነው።

ፓርኩ በ3.22 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ሲሆን፣ በውስጡ ሦስት ውብ ፋውንቴኖች (Fountains)፣ ዘመናዊ ስማርት ካፌቴሪያ፣ የትዕይንትና ዝግጅት ማቅረቢያ ስፍራ (Amphitheater) እና የተለያዩ ማረፊያ ቦታዎችን ያካተተ ነው። በተጨማሪም፣ ፓርኩ የተማሪዎችን የንባብ ባህል የሚያዳብር ምቹ አካባቢ ከመፍጠሩም በላይ ለተለያዩ ማህበራዊ ኩነቶች ማካሄጃነት ያገለግላል።

ዶ/ር አሥራት አፀደወይን የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ለሰጣቸው እውቅና የላቀ ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን፣ «እውቅናው መላው የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ በጋራ የሰራነው ውጤት በመሆኑ በዚያው ልክ እቀበለዋለሁ» ብለዋል። አክለውም «ትንሽ ሲሰሩ ብዙ ማመስገን የበለጠ አደራን የሚጥል በመሆኑ፣ ለማህበረሰቤ የሚኖረኝ አስተዋፅኦ የማይገደብና ወደፊትም የበለጠ እንድሰራ የሚያበረታታኝ ነው» ሲሉ ተናግረዋል።
ይህ ደረጃውን የጠበቀ ፓርክ በዶ/ር አሥራት አፀደወይን ስም መሰየሙ ተቋሙ ለባለውለታዎቹ የሚሰጠውን ከፍተኛ ክብር የሚያሳይ ከመሆኑም በላይ ለቀጣይ አመራሮችና ተመራማሪዎች ትልቅ የሰራ የመነሳሳት መንፈስ እንደሚፈጥር ታምኖበታል።

“ይህ ፓርክ ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ብቻ የተገደበ ሳይሆን፣ ለመላው የጎንደር ከተማ ነዋሪዎችም ክፍት በመሆን ዘመናዊ፣ ማራኪና ምቹ የመዝናኛ፣ የማህበራዊ ትስስርና የአገልግሎት ማዕከል ሆኖ ያገለግላል። ፓርኩ የዩኒቨርሲቲውንና የከተማውን ማህበረሰብ በማቀራረብ፣ ለመዝናኛ፣ ለማህበራዊ ትስስርና ለልዩ ልዩ ዝግጅቶች ምቹ ስፍራ ይሆናል። ይህም ፓርኩን ከመዝናኛ ቦታነት ባሻገር ለማህበረሰቡ ጠቃሚ የሆነ ዘመናዊ የአገልግሎትና የማህበራዊ ትስስር ማዕከል ያደርገዋል” ሲሉ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ልጃለም ጋሻው ተናግረዋል::

ዶ/ር አሥራት አፀደወይን የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ለሰጣቸው እውቅና የላቀ ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን፣ «እውቅናው መላው የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ በጋራ የሰራነው ውጤት በመሆኑ በዚያው ልክ እቀበለዋለሁ» ብለዋል። አክለውም «ትንሽ ሲሰሩ ብዙ ማመስገን የበለጠ አደራን የሚጥል በመሆኑ፣ ለማህበረሰቤ የሚኖረኝ አስተዋፅኦ የማይገደብና ወደፊትም የበለጠ እንድሰራ የሚያበረታታኝ ነው» ሲሉ ተናግረዋል።

ይህ ደረጃውን የጠበቀ ፓርክ በዶ/ር አሥራት አፀደወይን ስም መሰየሙ ተቋሙ ለባለውለታዎቹ የሚሰጠውን ከፍተኛ ክብር የሚያሳይ ከመሆኑም በላይ ለቀጣይ አመራሮችና ተመራማሪዎች ትልቅ የሰራ የመነሳሳት መንፈስ እንደሚፈጥር ታምኖበታል።

******************************************
ለልህቀት እንተጋለን!
የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ
ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም

ለዶ/ር አሥራት አፀደወይን የእውቅና እና የምስጋና፣ ለዶ/ር የቻለ ከበደ ደግሞ የእንኳን ደህና መጡ መርሃ ግብር ተካሄደ********************​የጎንደር ከተማ ማህበረሰብ ከጎንደር ዩ...
26/08/2026

ለዶ/ር አሥራት አፀደወይን የእውቅና እና የምስጋና፣ ለዶ/ር የቻለ ከበደ ደግሞ የእንኳን ደህና መጡ መርሃ ግብር ተካሄደ
********************
​የጎንደር ከተማ ማህበረሰብ ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ለቀድሞው የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ለዶ/ር አሥራት አፀደወይን የምስጋናና የእውቅና መስጠት፣ ለአዲሱ ፕሬዝዳንት ለዶ/ር የቻለ ከበደ ደግሞ የእንኳን ደህና መጡ መርሃ ግብር ዛሬ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ.ም አካሂዷል።

​በዚህ መርሃ ግብር ላይ የአዲሱ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር የቻለ ከበደ፣ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ዶ/ር አሥራት አፀደወይን፣ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው፣ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የቦርድ ም/ሰብሳቢና የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ተከተል ዮሐንስ፣ የማዕከላዊ ጎንደር ዞን አስተዳዳሪ አቶ አወቀ አስፈሬ፣ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ም/ፕሬዝዳንቶች፣ ጥሪ የተደረገላቸው የከተማዋ ከፍተኛ አመራሮች፣ የሃይማኖት አባቶችና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።

​የጎንደር ከተማ ማህበረሰብን በመወከል አቶ ሲሳይ አስማረ በመርሃ ግብሩ ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉ ሲሆን፣ ህብረተሰቡ ዩኒቨርሲቲውን እንደ ዓይኑ ብሌን የሚንከባከበው መሆኑን ገልጸው የተከናወኑ ዘርፈ-ብዙ ተግባራትን አብራርተዋል። አቶ ሲሳይ አክለውም ዶ/ር አሥራት አፀደወይን በሥራቸው ትጉህ፣ ሰው ወዳጅና ለአካባቢው ተቆርቋሪ ከመሆናቸውም በላይ ከማህበረሰቡና ከከተማ አስተዳደሩ ጋር ጠንካራ መስተጋብር የነበራቸው መሆኑን በመጥቀስ፣ ለአዲሱ ፕሬዝዳንት ለዶ/ር የቻለ ከበደ መልካም የሥራ ዘመን ተመኝተዋል።

​በተመሳሳይ መልኩ አንጋፋው መምህርና ተመራማሪ ፕሮፌሰር አምሳሉ ፈለቀ የጎንደር ዩኒቨርሲቲን ማህበረሰብ በመወከል የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።

​የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የቦርድ ም/ሰብሳቢና የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ተከተል ዮሐንስ በበኩላቸው በሰጡት ቁልፍ ንግግር፣ ዶ/ር አሥራት አፀደወይን በአመራርነት ዘመናቸው ያስመዘገቧቸውን ጠንካራ አፈጻጸሞች በዝርዝር አቅርበዋል። ለዚህ ውጤታማነት አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት በሙሉ ምስጋና ያቀረቡት ዶ/ር ተከተል፣ ለአዲሱ ፕሬዝዳንትም መልካም የሥራ ዘመን እንዲሆንላቸው ምኞታቸውን ገልጸዋል።

​የአሁኑ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንትና የቀድሞዋ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አሥራት አፀደወይን ባደረጉት ንግግር፤ ተቋማት ዘመናትን ተሻግረው እንዲዘልቁና የትውልድ ቅብብሎሻቸው እንዲቃና የተልዕኮ ፅናት፣ ከግለሰብ ተፅዕኖ የጸዳ ተቋማዊ አስተዳደርና አመራር እንዲሁም ስልታዊ ተለዋዋጭነት አስፈላጊ መሆናቸውን አስረድተዋል። አያይዘውም በአሁኑ ወቅት የሚመሩት የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ጋር በምርምር፣ በትምህርትና በማህበረሰብ ልማት ዘርፎች ተቀራርቦ ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን ገልጸው፣ በሥራ ዘመናቸው ለደገፏቸው የሥራ ባልደረቦቻቸውና ለመርሃ ግብሩ አዘጋጆች ምስጋና አቅርበዋል።

​የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር የቻለ ከበደ በመዝጊያ ንግግራቸው፣ መርሃ ግብሩ ለዶ/ር አሥራት ለሰጡት አገልግሎት እውቅናና ምስጋና ለማቅረብ ብቻ ሳይሆን እርሳቸው የጀመሯቸውን መልካም ሥራዎች አጠናክሮ ለማስቀጠልና የዩኒቨርሲቲውን የልህቀት ጉዞ ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር ቃል የሚገባበት ጭምር መሆኑን ገልጸዋል።

​ዶ/ር የቻለ አክለውም፣ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሴኔት ሰኔ 2017 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥ የሰራውን ሁለገብ ፓርክ "ዶ/ር አሥራት አፀደወይን ፓርክ" ተብሎ እንዲሰየም መወሰኑን አብስረው፣ ለዶ/ር አሥራት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

​በዚህ መርሃ ግብር ላይ በሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ የተዘጋጀና የዶ/ር አሥራትን ስኬታማ ሥራዎች የሚያስቃኝ አጭር ዶክመንታሪ የቀረበ ሲሆን፤ በፋሲለደስ የባህል ቡድን ባህላዊ ጭፈራዎች፣ መዝሙርና ግጥም ለሁለቱም ፕሬዝዳንቶች ከተለያዩ ተቋማትና ግለሰቦች በርካታ ስጦታዎች ተበርክተውላቸዋል።
​*********************
ለልህቀት እንተጋለን!
የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ
ነሐሴ 19/2018 ዓ.ም

እንኳን ለመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!*************************ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1501ኛው የነቢዩ መሐመድ ልደት (መውሊድ) በዓል በሰላ...
25/08/2026

እንኳን ለመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
*************************
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1501ኛው የነቢዩ መሐመድ ልደት (መውሊድ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
በዓሉ ሰላም፣ ፍቅርና በረከት የምናገኝበት ያድርግልን!
*************************
ለልህቀት እንተጋለን!
የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ
ነሐሴ 19/2018 ዓ.ም

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ወደ ራስ ገዝነት ለመሸጋገር ባደረገው ዝግጅት እና ቀሪ ሥራዎች ላይ ውይይት አካሄደ፡፡*******************በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት የስብሰባ አ...
24/08/2026

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ወደ ራስ ገዝነት ለመሸጋገር ባደረገው ዝግጅት እና ቀሪ ሥራዎች ላይ ውይይት አካሄደ፡፡
*******************
በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት የስብሰባ አዳራሽ፣ የዩኒቨርሲቲው የራስ ገዝ ሂደት ያለበትን ሁኔታ፣ እስካሁን የተከናወኑ ሥራዎችና ቀሪ ተግባራትን በተመለከተ ውይይት ተካሄደ። በመርሐ ግብሩም በራስ ገዝ ሂደቱ እስካሁን ስለተከናወኑ ሥራዎች ገለጻ ቀርቧል።

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር የቻለ ከበደ የመክፈቻ ንግግር ባደረጉበት በዚህ መድረክ፣ የራስ ገዝነት ለዩኒቨርሲቲዎች ዕድገትና ለተልዕኳቸው ስኬት ያለውን ፋይዳ አንስተዋል። ራስ ገዝነት ዩኒቨርሲቲዎች በትምህርት፣ በምርምር፣ በአስተዳደርና በሀብት አጠቃቀም የተሻለ አቅም እንዲገነቡና ለማኅበረሰቡ የሚሰጡትን አገልግሎት እንዲያጠናክሩ የሚያስችል አስፈላጊ መሠረት መሆኑንም ገልጸዋል።

በውይይቱ የራስ ገዝ ኮሚቴ አባላትና የዩኒቨርሲቲው አመራሮች ተሳትዋፈል:: በቀረበው ገለጻና በቀጣይ ሊከናወኑ በሚገባቸው ሥራዎች ዙሪያም ሀሳባቸውን በማንሳት ሰፊና ፍሬያማ ውይይት አድርገዋል። በውይይቱም ለቀጣዩ አንድ ዓመት የሚያገለግል የሥራ ማጣቀሻ ሰነድ ማዘጋጀት፣ ቀጣይ የሥራ አቅጣጫዎችን የሚያሳይ ዝርዝር የተግባር ዕቅድ ማውጣት እና እየተሰሩ ያሉ ሥራዎችን አፈጻጸም ለመከታተልና ለመገምገም በየሁለት ሳምንቱ ውይይት ማካሄድ ዋና ዋና የውይይት ነጥቦች ነበሩ።

በተነሱት ጥያቄዎችና ሀሳቦች ዙሪያ ሰፊ ውይይት ከተደረገ በኋላ፣የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር የቻለ ከበደ የራስ ገዝ ሂደቱ ስኬታማ እንዲሆን የሁሉም የጋራ ተሳትፎ፣ ቁርጠኝነትና ተጠያቂነት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። የተቀመጡ አቅጣጫዎች በተግባር እንዲፈጸም ሂደቱ በተቀናጀና በተከታታይ መንገድ እንዲቀጥል የሥራ መመሪያ በመስጠትም የዕለቱ የውይይት መርሐ ግብር ተጠናቋል።
*******************
ለልህቀት እንተጋለን!
የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ
ነሐሴ 18/2018 ዓ.ም

በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅና አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የምክክር መድረክ ተካሄደ***************************************በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ...
24/08/2026

በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅና አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የምክክር መድረክ ተካሄደ
***************************************
በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅና አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል መምህራን፣ የጤና ባለሙያዎችና የአስተዳደር ሰራተኞች በተገኙበት ነሐሴ 18/2018 ዓ.ም በማስተማሪያ ሆስፒታሉ ፕ/ር ያሬድ ወንድምኩን አዳራሽ የውይይት መድረክ ተካሂዷል።

የዚህ መርሀ-ግብር ዋና ዓላማ በተቋሙ የሚገኙ ዋና ዋና ጉዳዮችን በጋራ በመገምገም፣ ችግሮችን በውይይት ለመፍታትና የቀጣይ አቅጣጫዎችን በጋራ ለማስቀመጥ ያለመ ነው።

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር የቻለ ከበደ በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን፣ በንግግራቸውም የማስተማሪያ ሆስፒታሉ ተግባራት በተቀናጀና በተሳለጠ መንገድ እንዲከናወኑ ለማድረግ ሁሉም አካላት በትብብር መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።

የሆስፒታሉን አገልግሎት ጥራት ማሻሻልና ተቋሙ የሚጠበቅበትን የላቀ የህክምና፣ የትምህርትና የምርምር ሚና እንዲወጣ ማድረግ ቀዳሚ ትኩረት ሊሆን እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
በተለይም የአክሬዲቴሽን ሂደትን በተመለከተ ትኩረት ተሰጥቶ በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ ፕሬዚዳንቱ አክለው ጠቁመዋል።

በመድረኩ የምርምርና ትብብር ም/ፕሬዚዳንት ዶ/ር አይንሸት አደነ የተቋሙን የራስ አገዝ አሁናዊ ሁኔታ የሚመለከት ሪፖርትና ገለጻ አቅርበው በገለጻው ላይ የራስ ገዝ አሰራርን የበለጠ ለማጠናከርና የተቋሙን አቅም ሊገነባ በሚቻልባቸው አማራጮች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

በተጨማሪም የአስተዳደርና ልማት ም/ፕሬዚዳንት ረዳት አቶ ዘርፉ አቡሃይ እና የማስተማሪያ ሆስፒታሉ የሰራተኞች ድልድል ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ መልኬ ዓለሙ የሰራተኞች ድልድል ሂደት አሁን ያለበትን ደረጃና እስካሁን ያለፈበትን ሂደት የሚመለከት ገለጻ አቅርበዋል። በገለጻው መነሻነትም የሰራተኞች ድልድል ሂደትን የበለጠ ግልጽ፣ ፍትሃዊና ተቋማዊ አሰራርን ተከትሎ ለማስቀጠል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ሰፊ ምክክር ተደርጓል።

በውይይቱ የመድረኩ ተሳታፊዎች ሀሳቦቻቸውን፣ ጥያቄዎቻቸውንና ምክረ - ሀሳቦቻቸውን በማንሳት በተነሱት ጉዳዮች ላይ ግልጽ ውይይት ተካሂዷል።

በመጨረሻም ለተነሱት ጥያቄዎችና ሀሳቦችም በዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንትና ም/ፕሬዚዳንቶች ማብራሪያና ምላሽ እንዲሁም የቀጣይ የሥራ አቅጣጫ ተሰጥቶና መግባባት ላይ ተደርሶ መርሀ-ግብሩ ተጠናቋል ።
*******************
ለልህቀት እንተጋለን !
የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ
ነሐሴ 18/2018 ዓ.ም

Address

Maraki Street
Gondar

Opening Hours

Monday 08:00 - 17:00
Tuesday 08:00 - 17:00
Wednesday 08:00 - 17:00
Thursday 08:00 - 17:00
Friday 08:00 - 17:00
Saturday 08:00 - 17:00
Sunday 08:00 - 17:00

Telephone

+251581141232

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when University of Gondar posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The University

Send a message to University of Gondar:

Shortcuts

Share