08/05/2026
ወርልድ ብራይት ኮሌጅ ጽ/ቤት
በወንጌላዊ ታደሰ አበራ ህልፈት የተሰማውን ሀዘን ገለጸ
--- == -- ==
የወንጌል አርበኛና ትጉ አጋልጋይ ወንጌለዊ ታደሰ አበራ ሀቦሬ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።
ስረአተ ቀብራቸውም በሀድያ ዞን በጊምቢቹ ከተማ ቃለ-ህይወት ቤተክርስቲያን መከነ መቃብር ሥፍራ ተፈጽሟል።
ወንጌላዊ ታደሰ አበራ ሀቦሬ ከአባታቸው ከአቶ አበራ ሀቦሬ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ አዳነች ፎራጎ በሀድያ ዞን በቀድሞ በሶሮ ወረዳ በኩፋና ቀበሌ በ1956 ዓ.ም ተወለዱ።
ወንጌለዊ ታደሰ አበራ ሀቦሬ ዕድሜያቸው ለትምህት ስደርስ የ1ኛ ደረጀ ትምህርታቸውን በወንዶ-ገነት ቃ/ህ/ቤ/ያን፣ በወንዶገነት መከነ ኢየሱስ ቤ/ክ/ያን፣የ2ኛ ጀረጀ ትምህርታቸውን በጊምብቹ ከፍተኛ 2ኛ ደረጀ ት/ቤት ተከታትለዋል።
ወንጌለዊ ታደሰ አበራ በመንፈሳዊ ትምህርት ዘርፍም በቦቢቾ መጽሐፍ ቅዱስ ኮሌጅና በሆሳዕና እናት ቃ/ህ/ቤ/ያን በአማርኛና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎች በዲፕሎማና በዲግሪ ትምህርቱን ተከታትለው ተመርቋል።
ወንጌላዊ ታደሰ አበራ ሀቦሬ ገና በልጅነት ዕድሜያቸው የክርስትና እምነት ከተቀበሉ ከ1967 ዓ/ም ጀምሮ በተለያዩ መንፈሳዊ ዘርፎች ጠንካራና ለሌሎችም አርኣያ የሆኑ አገልጋይ ነበሩ።
ወንጌላዊ ታደሰ አበራ በወንዶገነት ከተማ ዙሪያ ፣በአሩሲ አውራጃና በሌሎችም አከባቢዎች የተለያዩ መንፈሳዊ አገልግሎቶች ደከመኝ ሰለቸኝ ሰይሉ በትጋትና በቆራጥነት ያገለገሉ መንፈሳዊ አባት እንደ ነበሩ የህይወት ታሪካቸው ይናገራል።
ወንጌላዊ ታደሰ አበራ በክርስትያኖች ላይ ስደትና መከራ በሚደርስበት በደርግ ዘመን የወቅቱን ስደት ፣ ዛቻ ፣ ማስፈራሪያና እስር ሳይፈሩ ራሳቸውን ለወንጌል የሰጡ ቆራጥ የወንጌል አርበኛ እንደነበሩም በህይወት ታሪካቸው ተመልክቷል።
ወንጌላዊ ታደሰ አበራ በጊምቢቹ ቃ/ህ/ቤ/ያን ከ1985 ዓ/ም ጀምሮ ህይወታቸው እስካለፈበት ጊዜ ድረስ ቤተክርስቲያኗን በወንጌል አገልግሎት፣በወንጌል ሥርጭት አስተባባርነት ፣በአስተማሪነት፣ በመሪነት እና በሌሎችም መንፈሳዊ አገልግሎቶች በአጠቃላይ ላለፉት 31 ዓመታት ምዕመናንን በታማኝነት ያገለገሉ ጠንካራ መንፈሳዊ አባት እንደነበሩም ይነገርላቸዋል።
ወንጌላዊ ታደሰ አበራ ከመንፈሳዊ አገልግሎታቸው ባሸገር በህዝብ ዘንድ በአስታራቅነት፣ በትህትና ፣በታማኝነት ፣በሰው ወዳድነትና አክባሪነት ፣በቅንነት ፣በጽኑ እምነት አቋምና፣ለሌሎች በመኖር የተመሠከሩ አባትም ነበሩ።
ወንጌላዊ ታደሰ አበራ ባደረባቸው ህመም ምንክያት በተለያዩ የህክምና አገልግሎት መስጫ ተቋማት በህክምና ስረዱ ቆይተው ሚያዝያ 27 /08/ 2018 ዓ.ም በተወለዱ በ62 ዕድሜያቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
የወንጌላዊ ታደሰ አበራ ሥርዓተ ቀብራቸውም ሚያዝያ 29/08/18 ዓ/ም በጊምቢቹ ከተማ ቃ/ህ/ቤ/ያን መካነ መቀብር ሥፍራ ዘመድ አዝማዶችና ወደጆቻቸው በተገኙበት ተፈጽሟል።
ወንጌላዊ ታደሰ አበራ ባለትዳርና የ2 ወንዶች እና የ3 ሴቶች በድምሩ የአምስት ልጆች አባት ነበር።
ወንጌላዊ ታደሰ አበራ ህልፈት የተሰማንን ሀዘን እየገለፀን ለወዳጅ ዘመዶቹ መፅናናትን እንመኛለን። ቤተሰቦቻቸው !!!
ዘገባው ፦
የወርልድ ብራይት ኮሌጅ የሕዝብ ግኑኝነት ዳሬክቶሬት ነዉ።
ዕለተ ሀሙስ ሚያዝያ 29/08/18 ዓ/ም
ጊምቢቹ