Injibara University

Injibara University Explore your Creative Potentials Explore your creative potentials

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የ2018 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎች የሜዳሊያና ዋንጫ ተሸላሚ፡-አላምረው ዋጋው - ከሶፍትዌር እንጂነሪንግ (Software Engineering) ትምህርት ክፍልበዩኒቨርሲቲ ቆ...
26/06/2026

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የ2018 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎች የሜዳሊያና ዋንጫ ተሸላሚ፡-

አላምረው ዋጋው - ከሶፍትዌር እንጂነሪንግ (Software Engineering) ትምህርት ክፍል

በዩኒቨርሲቲ ቆይታው ካጠናቀቃቸው 55 ኮርሶች ውስጥ 46 = A+ እና 9 = A በማምጣት ድንቅ ውጤት ያስመዘገበ የዩኒቨርሲቲው ልዩ ፈርጥ

በቀጣዩ የትምህርት ዘመን ከሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ መምህራን መካከል አንዱ ሆኖ በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የማስተማር ሥራን አሀዱ ብሎ ይጀምራል፡፡

ለአንተና ለመላው ቤተሰቦችህ እንዲሁም ለእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ መምህሮችህ እና የተምህርት ጓደኞችህ፡-

በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ!

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ፕሮግራሞች ያስተማራቸውን ተማሪዎች አስመረቀ፡፡ሰኔ 18/2018 ዓ.ም፤እንጅባራ ዩኒቨርሲቲዩኒቨርሲቲው ለ7ኛ ጊዜ በመደበኛ እና ተከታታይ መርሃ-ግብሮች በቅድመ ም...
25/06/2026

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ፕሮግራሞች ያስተማራቸውን ተማሪዎች አስመረቀ፡፡

ሰኔ 18/2018 ዓ.ም፤እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

ዩኒቨርሲቲው ለ7ኛ ጊዜ በመደበኛ እና ተከታታይ መርሃ-ግብሮች በቅድመ ምረቃ እና ድህረ- ምረቃ ያስተማረቸውን ተማሪዎች በድምቀት አስመርቋል፡፡

በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጋርዳቸው ወርቁ (ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው የአጠቃለይ ዘርፍ ዩኒቨርሲቲ በመሆን በአዋጁ የተሰጡትን ተልዕኮዎች ለማሳለጥ በሰባት ኮሌጆች፤ በሁለት ትምህርት ቤቶች እና በአንድ ኢንቲትዩት ተደራጅቶ ግብርና እና አረንጓዴ ልማትን፤ የህብረተሰብ ጤናን፤ ቱሪዝም እና ስራ ፈጠራን እንዲሁም የአገው ባህል፤ ቋንቋ እና ታሪክ የትኩረት መስኮቹ በማድረግ ልዩ ስትራተጂክ እቅድ በማዘጋጀት ወደ ትግባራ ምዕራፍ መሸጋገሩን ገልጸዋል፡፡

ዶ/ር ጋርዳቸው አያይዘውም ዩኒቨርሲቲው በ2018 የትምህርት ዘመን 14ሽ 470 ተማሪዎችን በ59 የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች፣ በ47 የ2ኛ ዲግሪ ፐሮግራሞች እና በ5 የ3ኛ ዲግሪ (PhD) ፕሮግራሞች በድምሩ በ110 ፕሮገራሞች በማስተማር በዚህ ዓመት ለ7ኛ ዙር 2 ሽ 903 ተማሪዎችን ማስመረቁን ተናግረው ከእነዚህ ውስጥ በአገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ በአገውኛ ቋንቋ እና ስነ-ጹሁፍ የመጀመሪያ ድግሪ ፕሮግራም ያስተማራቸውን 150 ተማሪዎች ማስመረቁን ገልፀዋል፡፡

ፕሬዝዳንቱ አክለውም በ2018 ዓ.ም የመጨረሻው ዓመት የመውጫ ፈተና ከተፈተኑ 53 ትምህረት ክፍሎች ውስጥ 43 ትምህርት ክፍሎች 50 ከመቶ በላይ ተማሪዎቻቸውን ያሳለፋ ሲሆኑ ከእነዚህ ውስጥ 15 ትምህርት ክፍሎች ማለትም Computer Scince, Chemistry, Mathematics, Statistics, Medical Laboratory, Nursing, Pediatrics and Child Health Nursing, Psychiatry, Food Science and Post-harvest-technology, Economics, Soft ware engineering, Management, Geography and Environmental studies, Sociology, Teacher education and curriculum study ትምህርት ክፍሎች 100 ፐርሰንት ተማሪዎች ማለፋቸውን ገልጸዋል፡፡

የእለቱ ክብር እንግዳ የሆኑት ገጣሚ፣ ሀያሲ፣ ደራሲ እና ጸሀፈ-ተውኔት ጋሽ አያልነህ ሙላቱ ለተመራቂ ተማሪዎች ባስተላለፉት ቁልፍ መልዕክት ዘመናዊ የምንለውን ሥርዓተ ትምህርት የምንፈጥረው ከውጭ ካገኘነው ልምድ ብቻ ተመስርተን በመገልበጥ ሳይሆን ወደ አገራችን ተመልክተን፣ አገር በቀል ዕውቀታችንን መሰረት ስናደርግ በመሆኑ ይህንንም ሥርዓተ ትምህርት ለማስተካከል የእናንተ የዛሬ ተመራቂዎች የወደፊት ሚና ትልቅ ነው በማለት ተመራቂ ተማሪዎች ሥልጣኔን የሚናፍቁ ወጣት ምሁራን በልዩነት ውስጥ አንድ ሆኖ ያሳደጋቸውን ማኅበረሰብ ባሕሉን ሳይበርዙ እና ሳይከልሱ፣ አገር በቀል ዕውቀቱን ከሕብረተሰቡ ተቀብለው ለቀጣዩ ትውልድ ማሸጋገር፣ በአገር በቀል ዕውቀት ላይ ዘመናዊ ሥልጣኔን የሚገነቡ እንዲሆኑ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

በመርሃ ግብሩ ተገኝተው ለተመራቂ ተሪዎች መልዕክት ያስተላለፉት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ አባል እና የአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዋና አስተዳደሪ ቴዎድሮስ እንዳለው በበኩላቸው "በራሱ ላይ የሚሰራ ትውልድ ሀገርን ይሠራል" ተመራቂዎችም ራሳቸው ላይ በመሥራት እና በየጊዜው አቅማቸውን በማሻሻል ለማኅበረሰቡ ስኬት እና እድገት እንዲሠሩ፤ ማኅበረሰባቸውን እና ሀገራቸውን በማገልገል ውለታ ከፋይ እንዲሆኑ፤ በቀጣይ ሕይወታቸው ራሳቸውን ከሁኔታዎች ጋር አላምደው በአመለካከት ራሳቸውን ገንብተው በሚሠማሩበ የሥራ መስክ ሀገራቸውን እና ማኅበረሰባቸውን እንዲያገለግሉ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

መርሃ ግብሩ በታላቅ ድምቀት ሲጠናቀቅ የ7ኛው ዙር የ2018 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎች ዋንጫ ተሸላሚ 4.00 በማስመዝገብ እና ከወሰዳቸው 55 ኮርሶች (46A+ እና 9A ) በማምጣት የሶፍትዌር ምንድህስና ተማሪ አላምራው ዋጋው የሁለት ሜዳሊያ እና የዋንጫ ተሸላሚ ሲሆን ከየኮሌጆች ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተመራቂ ተማሪዎችም የሜዲሊያ እና የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ከዚህ በፊት ለሙዚቃዋ ንግስት እጅጋየሁ ሽባባው (ጂጂ) የክብር ዶክትሬት ማበረክቱ የሚታወስ ሲሆን በዚህ ዓመትም ለዩኒቨርቲው እና ለሀገር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ለነበራቸው ጋሽ አያልነህ ሙላቱ አበጀ እና አባ ያዘው ዘለቀ ደስታ የምስጋና እና የእውቅና ሽልማት አበርክቶላቸዋል፡፡

በምረቃ ስነ ስርዓቱ ከዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች፣ የአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ከፍተኛ አመራሮች ፣ መምህራን፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የተማሪ ቤተሰቦች ተገኝተዋል፡፡

ያለህን እምቅ አቅም ለይተህ ተጠቀም!

25/06/2026
እንጅባራ ዩኒቨርስቲ  ለሀገር እና ለዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከቱ አንጋፋ ግለሰቦችን አመስግኗል ፡፡ሰኔ18/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ዩኒቨርሲቲው በ7ኛው ዙር የ2018 ...
25/06/2026

እንጅባራ ዩኒቨርስቲ ለሀገር እና ለዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከቱ አንጋፋ ግለሰቦችን አመስግኗል ፡፡

ሰኔ18/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

ዩኒቨርሲቲው በ7ኛው ዙር የ2018 ዓ.ም የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ምረቃ መርሀ-ግብር ላይ ለጋሼ አያልነህ ሙላቱ አበጀ እና አባ ያዘው ዘለቀ ደስታ የምስጋና እና የእውቅና ሽልማት አበርክቶላቸዋል ፡፡

በ7ኛው ዙር የ2018 ዓ.ም የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎች የዋንጫ ተሸላሚ 4.00  በማስመዝገብ እና ከወሰዳቸው 55 ኮርሶች (46A+ እና 9A )በማምጣት የሶፍትዌር ምህንድስና ተማ...
25/06/2026

በ7ኛው ዙር የ2018 ዓ.ም የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎች የዋንጫ ተሸላሚ 4.00 በማስመዝገብ እና ከወሰዳቸው 55 ኮርሶች (46A+ እና 9A )በማምጣት የሶፍትዌር ምህንድስና ተማሪ አላምራው ዋጋው ሆኗል ።
እንኳን ደስ አላችሁ!!

""የአገው ማኅበረሰብ ዛሬም ሆነ ቀደም ባሉት የታሪክ ዘመናት እራሱን በጥበብ፤ በሕንፃ ግንባታ፣ በእንስሳት ማላመድና ማዳቀል  ራሱን እያደራጀ የመጣ ሕዝብ ነው፡፡"ገጣሚ ሀያሲ፣ ደራሲ እና ጸ...
25/06/2026

""የአገው ማኅበረሰብ ዛሬም ሆነ ቀደም ባሉት የታሪክ ዘመናት እራሱን በጥበብ፤ በሕንፃ ግንባታ፣ በእንስሳት ማላመድና ማዳቀል ራሱን እያደራጀ የመጣ ሕዝብ ነው፡፡"ገጣሚ ሀያሲ፣ ደራሲ እና ጸሀፈ-ተውኔት ጋሽ አያልነህ ሙላቱ



ሰኔ 18/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ፕሮግራሞች ያስተማራቸውን ተማሪዎች በዛሬው ዕለት በታላቅ ድምቀት እያስመረቀ ይገኛል፡፡

የ7ኛው ዙር የእጅባራ ዩኒቨርሰቲ የተማሪዎች ምረቃ የዕለቱ ክብር እንግዳ ገጣሚ ሀያሲ፣ደራሲ እና ጸሀፊ ተውኔት ጋሽ አያልነህ ሙላቱ እንደተናገሩት አገው ማኅበረሰብ ዛሬም ሆነ ቀደም ባሉት የታሪክ ዘመናት እራሱን በጥበብ፤ በሕንፃ ግንባታ፣ በእንስሳት ማላመድና ማዳቀል፤ በግብርና ራሱን እያደራጀ የመጣ ሕዝብ መሆኑን ገልጸው ነገሥታቱ እራሳቸው አራሽ እና ተኳሽ፣ ንጉሥም፣ አንጋሽም፣ ቅዱስም በመሆን አሻራቸውን በአክሱምና በላሊበላ፣ በየአድባራቱ እና በየቤተ-መንግሥቱ በተጨባጭ አስቀምጠው ማለፈቸውን ተናግረዋል፡፡

ጋሼ አያልነህ አያይዘውም እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ዘመናዊውን የትምርት ሥርዓት ተከትሎ በዚህ መልክ መደራጀቱ ይበል የሚያሰኝ መሆኑንና ዩኒቨርሲቲው ይህን ሁሉ የታሪክ አደራ ተሸክሞ ግብርና እና አረንጓዴ ልማት፤ማኅበረሰብ አቀፍ ጤና፤ የአገው ሕዝብ ቋንቋ፣ ባሕል፣ ታሪክ እና አገር በቀል እውቀት እንዲሁም ቱሪዝም፣ ሥራ ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማትን የትኩረት መስክ አድርጎ መንቀሳቀሱ የሚያስመሰግነው እና በተጨባጭም ውጤት እያመጣ ለመሆኑ በዚህ ዕለት የሚመረቁ ተማሪዎች እና ተቋሙ ያከናወናቸው አያሌ ተግባራት ማሳያዎዎች መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ፕሮግራሞች ያስተማራቸውን ተማሪዎች በዛሬው ዕለት በታላቅ ድምቀት እያስመረቀ ነው፡፡ሰኔ 18/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲዪኒቨርሲቲው በመደበኛ እና ተከታታ...
25/06/2026

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ፕሮግራሞች ያስተማራቸውን ተማሪዎች በዛሬው ዕለት በታላቅ ድምቀት እያስመረቀ ነው፡፡

ሰኔ 18/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

ዪኒቨርሲቲው በመደበኛ እና ተከታታይ መርሃ ግብሮች በመጀመሪያ እና ሁለተኛ ዲግሪ ያስተማራቸውን ከ2ሽ900 በላይ ተማሪዎች ለ7ኛ ጊዜ በዛሬው ዕለት በታላቅ ድምቀት እያስመረቀ ይገኛል፡፡

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጋርዳቸው ወርቁ(ዶ/ር) እንጅባራ ዩኒቨርስቲ በ2018 ዓ/ም በመደበኛ፤ በተከታታይና በክረምት መርሀ ግብሮች በመጀመሪያ ድግሪ በ53 ፕሮግራሞች 1,770 ተመራቂዎች በሁለተኛ ዲግሪ በ19 ፕሮግራሞች 178 ተመራቂዎችን እንዲሁም በከፍተኛ ዲፕሎማ (HDP) 94 ተመራቂዎችን ፣ በማስተማር ስነ-ዘዴ (PGDT) 795 ተመራቂዎችን፣ በእንግሊዝኛ ማሻሻያ (ELIP) ፕሮግራም 66 ተመራቂዎችን፣ በድምሩ 2903 እጩ ተመራቂዎችን የሚያስመርቅ ሲሆን ከእነዚህ ተመራቂዎች ውስጥ 1130 (40%) ሴቶች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

ዶክተር ጋርዳቸው አያይዘውም ባለፋት ስድስት ዙሮች 9,100 ተመራቂዎችን በተለያዩ ፕሮግራሞች በማስመረቅ ለአገራችን እድገት የበኩሉን አሻራ እያሳረፈ ሲሆን የዚህን ዓመት ተመራቂዎች ጨምሮ ጠቅላላ የተመራቂዎች ቁጥር ከ12,ሽህ በላይ መድረሱን ተናገረው የዚህ ዓመት ምረቃ ላየት ሚያደርገው የ2018 ዓ/ም የተማሪዎችን ምረቃ ፕሮግራም የተለየ የሚያደርገው ዩኒቨርሲቲው ለመጀመሪያ ጊዜ በአራት ፕሮግራሞች ማለትም በአንስቴዠያ፣በሶፍትዌር ምህንድስና፣በመምህራን ትምህርት እና ካሪኩለም ጥናት እና በአገውኛ ቋንቋ እና ስነ-ጹሁፍ ፕሮግራሞች የሚያስመርቅ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ፕሬዝዳንቱ አክለውም እንጅባራ ዩኒቨርሰቲ በ2018 ዓ/ም ለመጀመሪያ ጊዜ (First sitters) ካስፈተናቸው የመደበኛ እና የተከታተይ ፕሮግራም ተፈታኝ ተማሪዎች መካከል በአማካይ 87.4 ከመቶ ተማሪዎችን በሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና (Exit exam) ያሳለፋ ሲሆን ይህም ከሀገራዊ የማለፍ ምጣኔ አንጻር እጅግ በጣም ከፍተኛ በመሆኑ ለዚህ ውጤት የበቁትን ተማሪዎች እና ያበቁትን መምህራንን አመስግነዋል፡፡

በምረቃ ስነ ስርዓቱ ገጣሚ ሀያሲ፣ደራሲ እና ጸሀፈ-ተውኔት ጋሽ አያልነህ ሙላቱ፣ የአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዋና አስተዳዳሪ እና የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ቦርድ አባል አቶ ቴዎድሮስ እንዳለውን ጨምሮ የብሄረሰብ አስተደዳሩ ከፍተኛ አመራሮች ፣የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች ፣ሴኔት አባላት፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የተመራቂ ቤተሰብ ወላጆች እየታደሙ ይገኛሉ፡፡

ውድ ተማሪዎች እና የተመራቂ ቤተሰቦች እንኳን ደስ አላችሁ!

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ፕሮግራሞች ሲያስተምር የነበራቸውን ተማሪዎች በዛሬው ዕለት በታላቅ ድምቀት እያስመረቀ ነው፡፡ሰኔ 18/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲዪኒቨርሲቲው በመደበኛ እ...
25/06/2026

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ፕሮግራሞች ሲያስተምር የነበራቸውን ተማሪዎች በዛሬው ዕለት በታላቅ ድምቀት እያስመረቀ ነው፡፡
ሰኔ 18/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
ዪኒቨርሲቲው በመደበኛ እና ተከታታይ መርሃ ግብሮች በመጀመሪያ እና ሁለተኛ ዲግሪ ሲያስተምር የነበራቸውን ከ2ሽ900 በላይ ተማሪዎች ለ7ኛ ጊዜ በዛሬው ዕለት በታላቅ ድምቀት እያስመረቀ ይገኛል፡፡
በምረቃ ስነ ስርዓቱ ገጣሚ፣ ሀያሲ፣ ደራሲ እና ጸሀፈ- ተውኔት ጋሽ አያልነህ ሙላቱ፣ የአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዋና አስተዳዳሪ እና የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ቦርድ አባል አቶ ቴዎድሮስ እንዳለውን ጨምሮ የብሄረሰብ አስተደዳሩ ከፍተኛ አመራሮች ፣የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች ፣ የሴኔት አባላት ፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የተመራቂ ቤተሰብ ወላጆች እየታደሙ ይገኛሉ፡፡
ውድ ተማሪዎች እና የተመራቂ ቤተሰቦች እንኳን ደስ አላችሁ!

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ፕሮግራሞች ሲያስተምር የነበራቸውን ተማሪዎች በዛሬው ዕለት ያስመርቃል፡፡ሰኔ 18/2018 ዓ.ም፤እንጅባራ ዩኒቨርሲቲዪኒቨርሲቲው በመደበኛ እና ተከታታይ መርሃ ግብ...
25/06/2026

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ፕሮግራሞች ሲያስተምር የነበራቸውን ተማሪዎች በዛሬው ዕለት ያስመርቃል፡፡
ሰኔ 18/2018 ዓ.ም፤እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
ዪኒቨርሲቲው በመደበኛ እና ተከታታይ መርሃ ግብሮች በመጀመሪያ እና ሁለተኛ ዲግሪ ሲስተምር የቆያቸውን ከ2ሽ900 በላይ ተማሪዎች ለ7ኛ ጊዜ በዛሬው ዕለት የተለያዩ እንግዶች በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ያስመርቃል፡፡
የምረቃ ስነ ስርዓቱ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላበአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በቀጥታ ይተላላፋል፡፡
ውድ ተማሪዎች እና የተመራቂ ቤተሰቦች እንኳን ደስ አላችሁ!

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የ7ኛ ዙር ተመራቂ ተማሪዎች የዋዜማ የመድረክ ዝግጅት  ውድ ተመራቂ ተማሪዎቻችን    እንኳን ደስ አላችሁ!        Congratulations!
24/06/2026

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የ7ኛ ዙር ተመራቂ ተማሪዎች የዋዜማ የመድረክ ዝግጅት
ውድ ተመራቂ ተማሪዎቻችን
እንኳን ደስ አላችሁ!
Congratulations!

Address

Injibara
40

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Injibara University posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The University

Send a message to Injibara University:

Share