16/08/2026
ከ10 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ለህብረተስብ ክፍሎች የንቃቴ ህግ ትምህርት ለመስጠት የዝግጅት መደረጉን የባስኬቶ ዞን ፍትህ መምሪያ አስታወቀ
#ገሊላ | ነሀሴ 10/2018 ዓ.ም(የኣሪ ማህበረሰብ ሬዲዮ)፦ የባስኬቶ ዞን ፍትህ መምሪያ ከ10 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ለህብረተስብ ክፍሎች "የንቃቴ ህግ ትምህርት" ለመስጠት የዝግጅት ማጠናቀቁን አስታውቀዋል።
የንቃተ ሕግ ትምህርት ዜጎች ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶቻቸውን፣ እንዲሁም ሕጋዊ ግዴታዎቻቸውን እንዲያውቁና እንዲረዱ ለማድረግ የሚሰጥ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት መሆኑን የባስከቶ ዞን ፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ ሚልክያስ ተናግዋል።
በተለያዩ የህግ ርዕሶች ላይ ለሚሰጠው የንቃተ ህግ ትምህርት የተዘጋጁ ስነዶች ከነሀሴ 11/2018 ዓ.ም እስከ ነሀሴ 15/2018 ድረስ "የንቃቴ ህግ ትምህርት" የሚሰጥ መሆኑን ያስታወቁት የመምሪው ኃላፊ ይህም በላስካ ዙሪያ ወረዳ እና በላስካ ከተማ ላይ ከ10ሺ በላይ ለምሆኑ ለህብረተስብ ክፍሎች ይሰጣል ብለዋል።
በላስካ ዙሪያ ወረዳ የግንዛበ ስራ በክላስተር የሚሰጥ ስሆን ይህም ኦብጫ ክላስተር፣ ዋጳ ክላስተር፣ ደብጻ ክላስተር እና ጋራ ክላስተሮች ከዚህ በፊት በተሰሩ ዳሰሳ ጥናት መሰረት የተለዩ እና ላስካ ከተማ ላይ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ ለመንግስት ሰራተኞዎች በየተቋማቱ የህግ ግንዛቤ ሥራዎች እንደምሰራ ጭምር አስታውቀዋል።
የዞኑ ፍትህ መምሪያ ኃላፊ ለዚህ ስራ ስኬት የመንግስት የስራ ኃላፍዎች እና መላው የከተማም ሆነ የዙሪያ ወረዳ ማህበረሰብ ክፍሎች ከፍትህ ተቋማት ጎን እንድሆኑ ጥሪ አቅርበዋል። መረጃው የዞኑ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ነው
ለተጨማሪ መረጃ ማህበራዊ ድህረ-ገፃችንን ይከታተሉ፦
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/AriCommunityRadioFm
ቴሌግራም፦ https://t.me/acrsfmAriCommunityRedioStationFM
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/aricommunityradiostation
ዩቲዩብ፦ https://www.youtube.com/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/.fm93.9
ዋትሳፕ፡- [email protected]" rel="ugc" target="_blank">https://whatsapp.com/[email protected]
ለበለጠ መረጃ(ጥቆማ)፦ በ0463212054, 0463212123, 04632122258, 0923126016 ላይ በመደወል አስፈላጊውን መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ።
የማህበረሰብ እውነተኛ ድምጽ !!
የኣሪ ማህበረሰብ ሬዲዮ ኤፍ ኤም 93.9