25/04/2026
ለሚዛን አማን ጤና ሳይንስ ኮሌጅ መምህራን የEffective Teaching Skill(ETS) እና Clinical Teaching Skill(CTS) ስልጠና ተሰጠ።
ሚያዚያ 17/2018 ዓ.ም: ሚዛን አማን
ለሚዛን አማን ጤና ሳይንስ ኮሌጅ መምህራን የEffective Teaching Skill(ETS) እና Clinical Teaching Skill(CTS) ስልጠና ተሰጠ። ስልጠናዉን በንግግር የከፈቱት የኮሌጁ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ዲን አቶ ሰብስቤ ኤሊያስ እንደተናገሩት ይህ ስልጠና መምህራኑ በሚያስተምሩበት ወቅት ደረጃውን የጠበቀ ትምህርት እንዲሰጡ የሚያስችል ስልጠና ነው ብለዋል።
ስልጠናው ከሚያዚያ 15 ቀን ጀምሮ ተከታታይ ለሶስት ቀናት ሲሰጥ የቆዬ ሲሆን ስልጠናው ለአዳዲስ መምህራን እና ደረጃቸውን አሻሽለው ከትምህርት ለተመለሱት መምህራኖች ሲሰጥ ቆይቷል።
ሰልጣኞቹ ይህ ስልጠና መሰጠቱ እንዳስደሰታቸው ገልፅው እንዲህ አይነት ስልጠና በይበልጥ ለአዲስ ተቀጣሪ መምህራን አስፈላጊ ስልጠና መሆኑን ተናግረዋል።
የኮሌጁ ዲን አቶ ፀጋዬ አትርሴ በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ ተገኝተው እንዳስተላለፉት ይህ ስልጠና መሰረታዊ የማስተማር ስነ ዘዴ መሆኑን ገልፀዉ በቀጣይ ሙያዊ ስልጠናዎች ተጠናክረዉ እንደሚቀጥሉ አመላክተዋል።
ለወቅታዊ መረጃ ማሕበራዊ ገፆቻችንን ይወዳጁ
Website፡ www.mahsc.edu.et
Facebook: https://www.facebook.com/fbMACOHS
Telegram: https://t.me/macohs2023