ሞጣ Poly Technic ኮሌጅ/Motta Poly Technic College

ሞጣ Poly Technic ኮሌጅ/Motta Poly Technic College ሞጣ ፖሌቴክኒክ ኮሌጅ

ቀን፦10/09/2018የሞጣ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2018 ዓ.ም የስልጠና ዘመን የግንቦት ወር የሙያ ብቃት ምዘና እየተሰጠ ይገኛል።የኮሌጁ ህዝብ ግንኙነት።
18/05/2026

ቀን፦10/09/2018
የሞጣ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2018 ዓ.ም የስልጠና ዘመን የግንቦት ወር የሙያ ብቃት ምዘና እየተሰጠ ይገኛል።
የኮሌጁ ህዝብ ግንኙነት።

የሞጣ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለሞጣ ከተማ መልካም ራዕይ የአካል ጉዳተኞች ማህበር የቢሮ መገልገያ እቃዎች እና የፅህፈት ቁሳቁስ አንድ ጠረጴዛ ፤አንድ አግዳሚ ወንበር፤አንድ ሸልፍ ፤አንድ ደስታ ወረ...
08/05/2026

የሞጣ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለሞጣ ከተማ መልካም ራዕይ የአካል ጉዳተኞች ማህበር የቢሮ መገልገያ እቃዎች እና የፅህፈት ቁሳቁስ
አንድ ጠረጴዛ ፤አንድ አግዳሚ ወንበር፤አንድ ሸልፍ ፤አንድ ደስታ ወረቀት እና አስራ ሁለት እስክርቢቶ ስጦታ ሰጥቷል።
ቀን ፦30/08/2018
የኮሌጁ ህዝብ ግንኙነት

የሞጣ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ መምህራን እና ሰራተኞች በስርዓተ-ፆታ እና ስሜታዊ ብልህነት ዙሪያ ስልጠና ወሰዱሞጣ (ሚያዝያ 20/2018 ዓ.ም)፡- የሞጣ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከ(FAWE)Ethiopia ...
28/04/2026

የሞጣ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ መምህራን እና ሰራተኞች በስርዓተ-ፆታ እና ስሜታዊ ብልህነት ዙሪያ ስልጠና ወሰዱ
ሞጣ (ሚያዝያ 20/2018 ዓ.ም)፡- የሞጣ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከ(FAWE)Ethiopia ጋር በመተባበር ለኮሌጁ አሰልጣኞች እና የአስተዳደር ሰራተኞች ያዘጋጀውን በGender Responsive Pedagogy የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ፡፡
የኮሌጁ ህዝብ ግንኙነት ባወጣው መረጃ መሰረት፤ ስልጠናው በዋናነት ትኩረቱን ያደረገው በሚከተሉት ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ነው፡-
• ስርዓተ-ፆታን ያማከለ የማስተማር ስነ-ዘዴ (Gender Responsive Pedagogy)
• ስሜታዊ ብልህነት (Emotional Intelligence)
ይህ ስልጠና የመማር ማስተማር ሂደቱን ስርዓተ-ፆታን ባማከለ መልኩ በማስኬድ የአሰልጣኞች እና የሰራተኞችን የስነ-ልቦና ዝግጁነት በማሳደግ የተቋሙን ተልዕኮ ለማሳካት ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ታምኖበታል።
________________________________________
የሞጣ ፖሊቴክኒክ ህዝብ ግንኙነት

የሞጣ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከሚያዚያ 13 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ  የዲጅታል አማራ ኢኒሸቲቨ የንቅናቄ ሳምንት በሚል የአካባቢውን ማህበረሰብ የዲጂታል ግንዛቤና ክህሎት ለማሳደግ ያለመ ሰፊ የሥል...
23/04/2026

የሞጣ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከሚያዚያ 13 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የዲጅታል አማራ ኢኒሸቲቨ የንቅናቄ ሳምንት በሚል የአካባቢውን ማህበረሰብ የዲጂታል ግንዛቤና ክህሎት ለማሳደግ ያለመ ሰፊ የሥልጠና መርሃ-ግብር ጀምሯል።
ይህ የዲጂታል አማራ ኢኒሼቲቭ (Amhara Initiative) የሥልጠና ፕሮግራም ዘመኑ የደረሰበትን የቴክኖሎጂ እውቀት ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተደራሽ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ ነው።
ስልጠናው ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ያካተተ ሲሆን፣ የሚከተሉት አካላት በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ፡-
• የኮሌጁ አሰልጣኞች፣ ሰልጣኞች እና የአስተዳደር ሰራተኞች፣
• በሞጣ ከተማ እና በ2 እጁ እነሴ ወረዳ የሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራንና ተማሪዎች፣
• የተለያዩ የሴክተር መሥሪያ ቤት ሰራተኞች፣
• ሥራ ፈላጊ ወጣቶች።
ስልጠናው በዘመናዊ ስማርት ፎኖች እና ኮሌጁ ባዘጋጃቸው የኮምፒውተር ላቦራቶሪዎች የሚሰጥ ሲሆን፣ በዋናነት በሚከተሉት አምስት የቴክኖሎጂ ዘርፎች ላይ ያተኩራል፡-
1. የይዘት ፈጠራ (Content Creation)
2. የድረ-ገጽ ልማት (Web Site Development)
3. የኔትወርክ ዝርጋታ (Networking)
4. ግራፊክ ዲዛይን (Graphic design )
5.ዲጅታል ማርኬቲንግ(Digital Marketing)
ይህ ስልጠናም በዲጅታል አለም ውስጥ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ ያስችላል።
15/08/2018 ዓ.ም

የሞጣ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለሁለት እጁ እነሴ ወረዳ አመራሮችና ለአጠቃላይ ሲቪል ሰርቪስ ሰራተኞች ስለ ዲጂታል ስኬል ስልጠና ምንነትና አስፈላጊነት የግንዛቤ ፈጠራ መድረክ አካሄደ።።።።።ሚያዚያ...
22/04/2026

የሞጣ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለሁለት እጁ እነሴ ወረዳ አመራሮችና ለአጠቃላይ ሲቪል ሰርቪስ ሰራተኞች ስለ ዲጂታል ስኬል ስልጠና ምንነትና አስፈላጊነት የግንዛቤ ፈጠራ መድረክ አካሄደ።
።።።።ሚያዚያ 14/08/2018 ዓ.ም።።።
በግንዛቤ ፈጠራ መድረኩ ላይ ተገኝተው የመግቢያ ንግግር ያደረጉት የሁለት እጁ እነሴ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማማሩ አይን አበባ ሲሆኑ ይህ የግንዛቤ ፈጠራ ስልጠና በዋናነት የዲጂታል አለምን በማዘመን ወቅቱ የሚጠይቀውን በቴክኖሎጅ የዳበረና ሁሉም ሲቪል ሰርቫንት ራሱን በዲጂታል ክህሎት በማብቃት የበለፀገች ሀገር መገንባት ይገባናል ሲሉ ተናግረዋል።
በሌላ በኩልም የግንዛቤ ፈጠራ ስልጠናውን የሰጡት የሞጣ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ አንዷለም የስጋት ሲሆኑ የስልጠናው ዋና አላማም የዲጂታል አለምን ሀገራችን በ2030 በቴክኖሎጂ የዳበረች እንድትሆንና እያንዳንዱ ዜጋ በዲጂታል አለም ውስጥ ብቁ ሆኖ እንዲገኝና የመንግስትን አሰራር ሙሉ በሙሉ በማዘመን በየመስሪያ ቤቱ የሚገኘውን የወረቀት ንክኪ የሌለበት አገልግሎት መፍጠር መቻል ነው ሲሉ ገልፀዋል ።

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች፣ ለኮሌጃችን ሰልጣኞች፣ ለአሰልጣኞች፣ ለአስተዳደር ሰራተኞችና ለአጋር አካላት በሙሉ እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል በ...
11/04/2026

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች፣ ለኮሌጃችን ሰልጣኞች፣ ለአሰልጣኞች፣ ለአስተዳደር ሰራተኞችና ለአጋር አካላት በሙሉ እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን።
የትንሳኤ በዓል ሞት ተረትቶ ሕይወት የሰለጠነበት፣ ተስፋ መቁረጥ አብቅቶ አዲስ ምዕራፍ የተበሰረበት ታላቅ የድል ቀን ነው። ቅዱስ መጽሐፍ “እርሱ ተነስቷል፤ በዚህ የለም” (ማቴዎስ 28:6) በማለት እንደሚነግረን፣ ትንሳኤ ለሰው ልጅ ሁሉ የድኅነት መንገድና ካለፈው ስህተት ታርሞ ወደ አዲስ ብርሃን የመሻገሪያ ምልክት ነው። ይህ በዓል በእኛ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ላለን ባለሙያዎች ትልቅ ትርጉም አለው፤ ይህም ማንኛውንም የቆየና የማይሰራ አሠራር በአዲስ የፈጠራ መንፈስና በቴክኖሎጂ በመተካት ለሀገርና ለወገን ብርሃን መሆን እንደሚገባን የሚያስተምር በመሆኑ ነው።
ኮሌጃችን ይህንን የአዲስ ተስፋ መንፈስ መሠረት በማድረግ፣ ለህብረተሰቡ የሚሰጠውን ጥራት ያለው ስልጠና፣ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር አገልግሎት ይበልጥ አጠናክሮ ይቀጥላል። በተለይም ማህበረሰብ አቀፍ ድጋፎችንና የበጎ አገልግሎት ስራዎችን እንደ አንድ ትልቅ ተልዕኮ በመውሰድ፣ የቴክኒክ ክህሎታችንን ለወገኖቻችን ችግር መፍቻነት ማዋል ይገባናል። የነገውን የቴክኖሎጂ ዘመን በንቃት ለመቀበልና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለመሆን የዲጂታል ክህሎት (Digital Skills) ወሳኝ መሆኑን በመገንዘብ፣ ኮሌጃችን በኦንላይን የሚሰጡ ዘመናዊ ስልጠናዎችን በስፋት እያመቻቸ ይገኛል። ስለሆነም አሰልጣኞች አስተዳደር ሰራተኞች ሰልጣኞችና ሌሎች ፍላጎቱ ያላችሁ የማህበረሰቡ ክፍሎች እነዚህን የዲጂታል ስልጠናዎች በመውሰድ ራሳችሁን ለዘመኑ ቴክኖሎጂ እንድታዘጋጁ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
ለኮሌጃችን ተልዕኮ መሳካት ሌት ተቀን እየደከማችሁ ያላችሁ የኮሌጁ አሰልጣኞች፣ የአስተዳደር ሰራተኞችና ሰልጣኞች፣ ላሳያችሁት ታላቅ አስተዋጽኦና የሥራ ተነሳሽነት በራሴና በኮሌጁ ስም ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን አቀርባለሁ። ይህ መልካም ተግባራችሁና ሙያዊ ግዴታችሁን የመወጣት መንፈስ በቀጣይም ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስባለሁ። የእናንተ ጥረት ኮሌጃችንን የልህቀት ማዕከልና ለለውጥ ምሳሌ ሊያደርገው እንደሚችል ቅንጣት ያህል ጥርጥር የለዉም። በጋራ በመሥራት የጀመርናቸውን የልማትና የቴክኖሎጂ ሽግግር ስራዎች ወደ ላቀ ደረጃ እንደምናሸጋግራቸው ሙሉ እምነት አለኝ።
በመጨረሻም፣ ፈጻሚ መስሪያ ቤቶች፣ የአጋር አካላትና የትምህርትና ስልጠና ቦርድ አባላት፣ ኮሌጃችን አዳዲስ እሳቤዎችንና ፖሊሲዎችን መሠረት በማድረግ የተሻለ አገልግሎት መስጠት እንዲችል በየደረጃው የምታደርጉትን ድጋፍ አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ ጥሪዬን አቀርባለሁ። የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የሀገር ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት እንደመሆኑ፣ የእናንተ እገዛ ለስኬታችን ወሳኝ ነው። በዓሉ የሰላም፣ የጤናና የፍቅር እንዲሆንላችሁ እየተመኘሁ፣ በድጋሜ እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ! እላለሁ፡፡

አንዱዓለም የስጋት
የኮሌጁ ዲን
ሚያዚያ 3 ቀን 2018 ዓ.ም

ከ8 ዓመት በላይ አገልግሎት መስጠት አቁሞ የነበረው ይህ ህንፃ ተገቢው የባለሙያ ጥናት ተደርጎለት እንደዚህ እየተጠገነ ነው።ሞጣ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ።
06/04/2026

ከ8 ዓመት በላይ አገልግሎት መስጠት አቁሞ የነበረው ይህ ህንፃ ተገቢው የባለሙያ ጥናት ተደርጎለት እንደዚህ እየተጠገነ ነው።ሞጣ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ።

ቀን 27/06/2018ዓ.ም የ"ዲጂታል አማራ" ስልጠና ንቅናቄን ለማሳካት ከአመራሩ ጋር ውጤታማ ውይይት ተካሄደየሞጣ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በክልላችን የተጀመረውንና የዜጎችን የዲጂታል ክህሎት ለማሳ...
07/03/2026

ቀን 27/06/2018ዓ.ም
የ"ዲጂታል አማራ" ስልጠና ንቅናቄን ለማሳካት ከአመራሩ ጋር ውጤታማ ውይይት ተካሄደ
የሞጣ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በክልላችን የተጀመረውንና የዜጎችን የዲጂታል ክህሎት ለማሳደግ ያለመውን "ዲጂታል አማራ" የተሰኘ ግዙፍ የክህሎት ማበልጸጊያ ፕሮግራም በስኬት ለመተግበር ከአመራር አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሂዷል። በመድረኩ ላይ የከተማ አስተዳደሩ የከንቲባና የቀበሌው አመራሮች ተገኝተዋል። በውይይቱም የሚከተሉት ዋና ዋና ነጥቦች ላይ ግንዛቤ ተፈጥሯል፦
 ቁልፍ የውይይት ነጥቦች
• የኮሌጁ ሚና፦ ኮሌጁ በክልሉ ካሉ 42 ኮሌጆች መካከል ይህን ስልጠና እንዲሰጡ ከተመረጡ 18 የፓይለት ኮሌጆች አንዱ በመሆኑ፣ የተሰጠውን ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት ስላለው ዝግጅት።
• የስልጠናው ይዘት፦ ስልጠናው በዘመናዊ የኦንላይን ፕላትፎርም የሚሰጥ ሲሆን፤ በይዘት ፈጠራ፣ በዲጂታል ማርኬቲንግ፣ በግራፊክ ዲዛይን፣ በኔትዎርክ ዝርጋታና በድህረ-ገጽ ልማት ላይ እና መሰረታዊ ነካከለኛና ከፍተኛ የዲጂታል ክህሎት: ላይ ያተኮረ መሆኑን።
• ወቅታዊ አፈጻጸም፦ እስካሁን 642 ሰልጣኞች የተመዘገቡ ሲሆን፣ ከእነዚህም ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ስልጠናውን መጀመራቸው ተገልጿል።
• የመሠረተ-ልማት ዝግጅት፦ ኮሌጁ ስማርት ፎን ወይም ላፕቶፕ ለሌላቸው ሰልጣኞች የኮምፒውተር ላቦራቶሪዎችን ክፍት ማድረጉ ተመላክቷል።
 የአመራሩ ቁርጠኝነት የከተማውና የቀበሌ አመራሮች የቀረበውን ጥሪ በመቀበል፣ ፕሮግራሙን ከግብ ለማድረስ የሚከተሉትን ውሳኔዎች አሳልፈዋል፦
1. አርአያነት፦ አመራሩ ራሱ በስልጠናው በመሳተፍ ለህዝቡ አርአያ ለመሆን።
2. ንቅናቄ፦ ከነገ ጀምሮ በየቀበሌው የሚገኙ ስራ ፈላጊዎችን፣ ተማሪዎችንና የመንግስት ሰራተኞችን ወደ ስልጠናው እንዲገቡ የማቀስቀስና የማመቻቸት ስራ ወደ ተግባር እንዲገባ። በመጨረሻም፣ አመራሩ ስልጠናውን በማፋጠንና ህዝቡን በማንቀሳቀስ ረገድ የበኩሉን ድርሻ ለመወጣት ሙሉ ስምምነት ላይ ደርሷል።
"የዲጂታል ክህሎት ለተወዳዳሪነትና ለፈጣን ዕድገት!"
የሞጣ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ

የሞጣ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የህብረተሰቡን ችግር ሊፈታ የሚችል የፕላስቲክ ጠርሙስ መሰንጠቂያ ማሽን ቴክኖሎጂ በመቅዳት ለተጠቃሚዎች ለማድረስ በሞጣ ከተማ አስተዳደር ስር ለሚገኙ 16 ለተመረጡ አ...
27/02/2026

የሞጣ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የህብረተሰቡን ችግር ሊፈታ የሚችል የፕላስቲክ ጠርሙስ መሰንጠቂያ ማሽን ቴክኖሎጂ በመቅዳት ለተጠቃሚዎች ለማድረስ በሞጣ ከተማ አስተዳደር ስር ለሚገኙ 16 ለተመረጡ አብዥ ኢንተርፕራይዞች የቴክኖሎጂውን ሙሉ ሰነድና የተግባር ስልጠና ሰጥቷል። ይህ ቴክኖሎጅም ለኮፍያ ፣ለቁም መጥረጊያ ፣ለዘንቢል መስሪያ እና ለተለያዩ የእደጥበብ መስሪያ የሚውል ግብአት ያመርታል።

የምስጋና መግለጫ!!በኮሌጃችን የእንጨት ሥራ ዘርፍ የሚገኙ አሰልጣኞች ባሳዩት ከፍተኛ የሙያ ክህሎት እና ትጋት የተመረቱት ሶፋና ቁም ሳጥን የኮሌጃችንን አቅም በተግባር ያሳዩ ሆነዋል።ለዚህ ው...
25/02/2026

የምስጋና መግለጫ!!
በኮሌጃችን የእንጨት ሥራ ዘርፍ የሚገኙ አሰልጣኞች ባሳዩት ከፍተኛ የሙያ ክህሎት እና ትጋት የተመረቱት ሶፋና ቁም ሳጥን የኮሌጃችንን አቅም በተግባር ያሳዩ ሆነዋል።
ለዚህ ውጤት መገኘት፦
ጥበባቸውን እና ላባቸውን ላፈሰሱ የእንጨት ሥራ አሰልጣኞቻችን፣
በሃሳብ እና በምክር ለደገፋችሁ ባለሙያዎች፣
እንዲሁም ጥራቱን የጠበቀ ግብዓት (Material) በወቅቱ ላቀረባችሁ የግዥ ባለሙያዎቻችን፣
ኮሌጁ ያለውን ጥልቅ ምስጋና ያቀርባል። ይህ የጋራ ስራ እና ውጤት ተጠናክሮ ይቀጥላል!
"ጥራት ያለው ስልጠና ለተግባራዊ ውጤት!"

Address

Motta

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሞጣ Poly Technic ኮሌጅ/Motta Poly Technic College posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share