28/02/2025
የካቲት 20፣ 2017 ዓ.ል | ሻዕባን 29 ፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ጨረቃ አርብ ምሽት ከታየች የ1446 ዓ.ሒ የታላቁ ረመዷን ፆም ቅዳሜ ካልታዬች ግን እሁድ እንደሚሆን ጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤት ገለፀ።
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |
የፌደራል ጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤት ለጠቅላይ ምክር ቤቱ በላከው መግለጫ ጨረቃ አርብ የካቲት 21/17 ( ሻዕባን 29/1446) ከታየች የ1446 ዓ.ሒ የታላቁ ረመዷን ፆም ቅዳሜ የካቲት 22/17 ዓ.ል የሚጀመር ሲሆን፤ ካልታየች ግን የረመዷን ፆም እሁድ የካቲት 23/17 ዓ.ል እንደሚጀምር ገልጧል።
ለተከበረው የረመዷን ወር ፆም በሰላም ላደረሰን አሏህ ምስጋና እናቀርባለን ያለው የጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤቱ መግለጫ ህዝበ ሙስሊሙ በፆም ወቅት ኢስላማዊውን የመደጋገፍና የመረዳዳት ተግባር የበለጠ አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤቱ አደራ ብሏል።
በመጨረሻም ለሐገራችን እና ለመላው ዓለም ህዝበ ሙስሊም ፆሙ የጤና፣ የሰላምና የፍቅር እንዲሆን ጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤቱ መልካም ምኞቱን ገልጿል።
••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት።
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1