KCIC ቃኮኢኮ ⁻ Kawakoto Construction And Industrial College

KCIC ቃኮኢኮ ⁻ Kawakoto Construction And Industrial College To create work creater

ማስታወቂያ ለትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ!!‼️የቃውቆቶ ኮንስትራክሽን እና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ እንኳን ለ2015 የስልጠና ዘመን በሰላም አደረሳችሁ እያለ ለነባርና ለአዳዲስ ሰልጣኞች ምዝገባ የሚ...
04/10/2022

ማስታወቂያ ለትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ!!‼️

የቃውቆቶ ኮንስትራክሽን እና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ እንኳን ለ2015 የስልጠና ዘመን በሰላም አደረሳችሁ እያለ ለነባርና ለአዳዲስ ሰልጣኞች ምዝገባ የሚካሄደው ከመስከረም 25/2015 ዓ ም ጀምሮ መሆኑን እያሳወቀ ስልጠና የሚጀምረው ጥቅምት 1/2015 እንደሆነ ያስታውቃል ።

ማሳሰቢያ ፦ በ2015 አዲስ የሚመዘገቡ ሰልጣኞች በስራና ክህሎት ሚንስቴር በተቀመጠው የመመዝገቢያ መስፈርት መሰረት የ12ኛ ክፍል ዶክመንት ያላቸው ብቻ መሆኑን በማሳወቅ ለምዝገባ ሲመጡ 02 ጉርድ ፎቶ ግራፍ መያዝ ይኖርባቸዋል ።

👉ስልጠና የሚሰጥባቸው ዲፓርትመንቶች:-

➧በኮንስትራክሽን ከደረጃ አንድና ሁለት

➧በቤዚክ ሜታል ወርክ ( በብረታ ብረት በደረጃ አንድና ሁለት

➧በኢንፎርሜሽን ኮምኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT) በደረጃ አንድ ሁለትና ሶስት

➧በጋርመንት ልብስ ስፌት በደረጃ አንድ ሁለትና ሶስት

➧በፈርኒቸር እንጨት ስራ በደረጃ አንድ መሆኑን ይገልጻል ።

የኮሌጁ ሪጅስተር

(አልቾ ኮሚኒኬሽን)

28/06/2022
የቃዋቆቶ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ፤ሰኔ 17/2014 ዓ.ም መደበኛ ሰልጣኞችን፣ ኢንተርፕራይዞች፣ በግል የብቃት ማረጋገጫ ለመውሰድ የተመዘገቡ ሰርቫንቶችን ከሲኦሲ ኤጀንሲ ጋር በመሆ...
26/06/2022

የቃዋቆቶ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ፤
ሰኔ 17/2014 ዓ.ም መደበኛ ሰልጣኞችን፣ ኢንተርፕራይዞች፣ በግል የብቃት ማረጋገጫ ለመውሰድ የተመዘገቡ ሰርቫንቶችን
ከሲኦሲ ኤጀንሲ ጋር በመሆን በኤጀንሲው ተመድበው በመጡ ፈታኞች አማካኝነት አስመዝኗል።

በዚህም መሰረት ምዘናው የተሰጠባቸው 06 የሙያ መስኮች ሲሆኑ፥ እነዚያም
ብረታብረት፣ ፈርኒቸር፣ ኮንስትራክሽን፣ ጋርመንት፣ አይሲቲ እና አካውንቲንግ ናቸው።

የብቃት ማረጋገጫ ምዘና ለመውሰድ ከተመዘገቡ 89 ተመዛኞች፤ 83 ምዘናውን የወሰዱ ሲሆን 81 ብቁ መሆን ችሏል።

ምሁራን የሀገርን ሰላም ለማረጋገጥ የመፍትሔ ሀሳቦችን በማቅርብ የበኩላቸውን ልወጡ ይገባል።               ግንቦት 9/2014 ዓ.ም ቃዋቆቶ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ~~~~~...
18/05/2022

ምሁራን የሀገርን ሰላም ለማረጋገጥ የመፍትሔ ሀሳቦችን በማቅርብ የበኩላቸውን ልወጡ ይገባል።
ግንቦት 9/2014 ዓ.ም
ቃዋቆቶ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
"የዜጎች ቀጥተኛ ሚና ለሁለንተናዊ ብልፅግና" በሚል መሪ ቃል በቃዋቆቶ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ በሀገራዊ፣ ክልላዊና ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከአጠቃላይ አስተዳደር ሰራተኞች እና አሰልጣኝ መምህራን ጋር ውይይት ተካሂዷል።

ያለ ዜጎች ቀጥተኛ ተሳትፎ በሁሉም መስክ የተሳካላት ሀገር መፍጠር አይቻልም በሚል ሀሳብ ዙሪያ በተዘጋጀ ሠነድ ላይ ጠለቅ ያለ ውይይት የተደረገ ሲሆን፤
የውይይት መነሻ ነጥቦችን በዝርዝር ያቀረቡት የኮሌጁ ዲን አቶ ባህረዲን ከድር- ምሁራን ለሀገር አንድነትና ሰላም ለማረጋገጥ የመፍትሔ ሀሳቦች በማቅርብ በሀገር ግንባታ ላይ ወሳኝ ሚና እንዳላቸው በማንሳት ምሁራን በእውቀትና ክህሎት የተመሰረተ የሰላም መንገድ ሊያመጡ የሚችሉ የመፍትሔ ሀሳቦች በማቅርብ ለሀገር አንድነትና ሰላም ለማረጋገጥ የበኩላቸውን በመወጣት መንግስትንና ሃገርን ማገዝ እንደሚገባቸውም ገልጸዋል።

አክለውም ዲኑ እንደገለጹት የሃገር ጉዳይ ሁሉንም ዜጋ የሚመለከተው ቢሆንም ከምሁራን የሚፈልቁ እውቀትን መሰረት ያደረጉ የመፍትሔ ሃሳቦችን እንደ ግብዓት በመጠቀም የሀገርን አንድነትና ሰላም ለማረጋገጥ ወሳኝ ስለሆነ ከውይይት በመፍትሄ አማራጮች ላይ ግብዓት ለማግኘት የሚረዳ መሆኑንም ገልጸዋል።
~~~~~~~
ለውይይቱ የቀርበውን ሰነድ መነሻ በማድረግ ተሳታፊዎች ሃሳብ እና ጥያቄዎችን በማንሳት ሰፊ ምክክር ያደረጉ ሲሆን፤
አገራዊ ለውጡ የሀገራችንን ምሁራንና ወጣቶችን ጨምሮ በሁሉም ኢትዮጵያውያን መስዋዕትነት ላይ ተመስርቶ የተጀመረ ህዝባዊ ለውጥ እንደመሆኑ መጠን፤ ከፍተኛ ጥንቃቄና በዕውቀት የተመሰረተ የመፍትሔ ሃሳብ ፣ ከስሜታዊነት የተላቀቀና የሰከነ አመለካከት በተለይ ሁኔታ የምሁራን ተሳትፎ የሚፈልግ በመሆኑ የቃዋቆቶ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅም ስራ ፈጣሪ ትውልድ ማምረት የሚችል ተቋም በመሆኑ ሰራተኞች የበኩላቸውን ድርሻ መወጣት እንደሚገባቸው ተሳታፊዎች ባቀረቧቸው ሃሳቦች ላይ አመላክተዋል።

በተያያዘም ተሳታፊዎች ከምንም በላይ በአሁን ሰዓት ሀገራችን ወደ ብልፅግና ጉዞ በምታደርግበት በዚህ ወቅት የሀገራችን ሰላም የማይፈልጉ የሃይማኖት እና የብሄር አክራሪዎች የተለያዩ አጀንዳዎችን እየቀረፁ ህዝብ ለህዝብ ለማጋጨት አቅደው ከማህበራዊ ሚዲያ ጀምሮ የሃሰት መረጃዎችን በማሰራጨት ጭምር ችግር እየፈጠሩ በመሆኑ ሁሉም ዜጋ ለሀገራችን አንድነትና ሰላም ሲባል የድርሻውን መወጣት ያለበት ቢሆንም ምሁራን የማህበራዊ ሚዲያውን የሃሰት መረጃውን በተጨባጭ እውነት ላይ በተመሰረተ መረጃ ከመመከት ጀምሮ ትልቁን ድርሻ እንደሚይዙም ተሳታፊዎች ከነሱት አስተያየትና ባቀረቧቸው ሃሳቦች ገልጿል።
~~~~~~
በመጨረሻም ለተነሱ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች በኮሌጁ ዲን በአቶ ባህረዲን ከድር በተነሱ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያና ምላሾች ሰጥተው፤ ውይይቱ በአጠቃላይ ሀሳቦችን ሁሉም በነጻነት በማንሳት በጥሩ ሁኔታ መግባባት ተችሎ የውይይት መድረክ ተጠናቋል።

ግንቦት 09/2014 ዓ.ም
ቃዋቆቶ ኮንስትራክሽንና በኢንዱስትሪያል ኮሌጅ

ከቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት አመራሮች ጋር የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው***************የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከግልና መንግስታዊ ያልሆኑ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት አመራ...
06/04/2022

ከቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት አመራሮች ጋር የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው
***************
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከግልና መንግስታዊ ያልሆኑ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት አመራር ጋር በተቋሙ ቁልፍ ተልዕኮዎች ፣ የሪፎርም ተግባራትና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ የምክክር መድረክ እያካሄደ ነው።

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ በከር ሻሌ(ዶ/ር) ባለፋት ሁለት አስርት ዓመታት ለግሉ ዘርፍ ገበያው ክፍት በመደረጉ ሰፋፊ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ተከፍተዋል። በዚህም የስልጠና ተደራሽነትን ማረጋገጥ በመቻሉ የግሉ ዘርፍ ላበረከተው አስተዋፅኦ አመስግነዋል።

የስልጠና ጥራት ትኩረት ሰጥተን የግልም ሆነ የመንግስት ተቋማት ተረባርበን በመስራት ክህሎት ያለው ፣ ሥራ ፈጣሪና አምራች ኃይል መፍጠር ይጠበቅብናል። ውይይቱ መሰረታዊ የፖሊሲ ለውጦች ላይ ተመሳሳይ ግንዛቤ እንዲኖር ከመንግስት ተቋማት በተለየ መዘጋጀቱንም ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ የግል ፣ ከፍተኛ ትምህርትና ቴክኒክና ሙያ ተቋማት ማህበር ፕሬዚዳንት ሞላ ፀጋዬ (ዶ/ር) የትምህርት ጥራትን በተመለከተ ብዙ መሥራት እንዳለብን እንገነዘባለን በዚህም ላይ አብረን እንሰራለን ብለዋል።

ከተለያዩ ክልሎች ለመጡት የውይይቱ ተሳታፊዎች ስለሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ተልዕኮና አደረጃጀት ገለፃ ማድረጉን ሚኒስቴሩ ገልጸዋል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼
(ኢ ፕ ድ)

በቃ/ኮ/ኢ/ኮ ለአሰልጣኝ መምህራንና ለአስተዳደር ሰራተኞች በሥነ ምግባርና በብልሹ አሰራር ዙሪያ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ፡፡                ● መጋቢት 22/2014 ዓ...
31/03/2022

በቃ/ኮ/ኢ/ኮ ለአሰልጣኝ መምህራንና ለአስተዳደር ሰራተኞች በሥነ ምግባርና በብልሹ አሰራር ዙሪያ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ፡፡
● መጋቢት 22/2014 ዓ.ም ቃ/ኮ/ኢ ኮሌጅ

◎ በስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ የቃዋቆቶ ኮንስትራክሽን እና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ፦ በሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና አዋጆችና ደንቦች፣ የአመራርነትና ሙያዊ ሥነ-ምግባር እና ዓለም አቀፋዊ ፀረ-ሙስና በተመለከተ ለአሰልጣኝ መምህራንና ለአስተዳደር ሰራተኞች ስልጠና የተሰጠ ሲሆን ስልጠናው በዋናነት በስነ ምግባርና በብልሹ አሰራር ዙሪያ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እንዲሁም ከዚህ ጋር ተያያዥነት ልኖራቸው በሚችሉ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች፤ የቅድመ የመከላከል ዘዴዎች፤ የሚፈቱበት ዘዴዎች እና ሌሎችም ተያያዥነት ባላቸው ጉዳዮች ላይ ለአሰልጣኝ መምህራንና ለአስተዳደር ሰራተኞች ተሰጥቷል።

◍ስልጠናውም በስልጤ ዞን ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና መምሪያና ትብብር በመጠየቅ በተላከልን በመምሪያው የሥነ ምግባር ኦፊሰር አሰልጠኝነት የተሰጠ ነው።

¤ የስልጠናው አጀማመርን በተመለከተ የመክፈቻ መልዕክት ያስተለፉት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ በህረዲን ከድር ይህ ስልጠና የሚሰጥበት አበይት ጉዳይ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ሽፋንን ለማሳደግ፤ በዚህም የሚታዩ ኋላቀርና ፀረ-ልማት አስተሳሰቦችን በመልካም ስነ-ምግባር የተገነባ፣ ሙስናን የሚፀየፍ በፅናት የሚታገል ሰራተኛን ለመፍጠር ያስችል ዘንድ የታለመ መሆኑን የገለፁ ሲሆን በፀረ-ሙስና አዋጆች ላይ እና ሙያዊ ሥነ-ምግባር እንዲሁም በብልሹ አሰራር ዙሪያ ግንዛቤ ለማስጨበጥና ሰራተኛውን ለማነቃቃት ነው ያሉት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ባህረዲን
በንግግራቸውም አያይዘው የእኛ የትምህርት ዘርፍ ላይ በሀሰተኛ ትምህርት ማስረጃ፣ የፈተና ስርቆሽ፣ የትምህርት(የስራ) ሰዓት መሸራረፍ፣ የግዢ ሂደት ውስጥ እና ሌሎችም መገለጫዎች ላይ ልከሰት እንደሚችል በመጥቀስ፤ ሙስናና ብልሹ አሰራር እንደሀገር ስር ሰዶ የተንሰራፋ እንዳይሆን ከተቋማችን ጀምረን በሚስተዋሉ በሙስና፣ በስነ ምግባርና ብልሹ አሰራር ችግሮችና የተሳተፉ ሰዎች ላይ የሚወሰዱ እርምጃዎች አናሳ እንደማይሆኑ በማሳሰብ፣ የስራ ኃላፊዎችም ሆነ ሌሎች ሰራተኞች የስነ ምግባር ጥሰትንና ብልሹ አሰራርን በተመለከተ ሁሉም በአንድነት ተጋግዘው በመስራት የጋራ ውጤት ልኖራቸው ይገባልም ብሏል።

~ በሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና አዋጆችና ደንቦች፣ የአመራርነትና ሙያዊ ሥነ-ምግባር እና ዓለም አቀፋዊ ፀረ-ሙስና በተመለከተ ለአሰልጣኝ መምህራንና ለአስተዳደር ሰራተኞች፥ በዋናነት በስነ ምግባርና በብልሹ አሰራር ዙሪያ የተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና የሰጡት የስልጤ ዞን ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና መምሪያ ሥነ-ምግባር ኦፊሰር/ዳይሬክቶሬት አቶ ሙዴ ሁሴን ሲሆኑ ዳይሬክቶሬቱ ዋና ዋና ተግባራት ያሏቸው ማስተማር፣ መከላከል እና ህግ ማስከበር መሆናቸውን በማውሳት፤ ስነ ምግባርና ብልሹ አሰራርን በተመለከተ ፣ የሙስና አይነቶች፣ ሙስና የሚያስከትላቸው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች እና የሙስና አዋጆች ላይ ገለፃ ያደረጉት አቶ ሙዴ ሁሴን በተለይ በአመራርነትና ሙያዊ ሥነ-ምግባር ዙሪያ በገለፃቸው የሥነ-ምግባር ፅንሰ ሃሳቦች፣ ስነ-ምግባራዊ አመራርነት፣ የትምህርት አመራር ሚና ለብልሹ አሰራር በሚሉት እና በሌሎች ሃሳቦች ዙሪያ ማራኪ በሆነ መንገድ ገለፃ አድርገዋል። ተሳታፊዎችም በርዕሱ ዙሪያ ሰፋ ያለ ግንዛቤ እንዳገኙ ገልፀዋል።
◈መጋቢት 22/2014 ዓ.ም
ቃዋቆቶ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ

የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን ለመደገፍና ከስደት ተመላሾችን ማቋቋም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ተካሄደ*******************የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር በአማራና አፋር ክልሎች ጉዳት የ...
30/03/2022

የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን ለመደገፍና ከስደት ተመላሾችን ማቋቋም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ተካሄደ
*******************
የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር በአማራና አፋር ክልሎች ጉዳት የደረሰባቸውን ኢንተርፕራይዞች፣ የቴክኒክና ሙያ ተቋማትንና ከስደት ተመላሾችን ማቋቋም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ዓለማቀፍ ተቋማት ጋር ውይይት አካሂዷል፡፡

ከስደት ተመላሽ ዜጎችን በተመለከተ የችግሩን ግዝፈት የሚያመላክት መነሻ ፅሁፍ ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል፡፡

በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ፣ ሥራ ስምሪት እና ገበያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ንጉሡ ጥላሁን፣ የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ በከር ሻሌ (ዶ/ር) እንዲሁም በገንዘብ ሚኒስቴር የኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስትር ዴኤታ ሰማሪታ ሰዋሰው ውይይቱን መርተውታል።

ያጋጠሙት ችግሮች መንግስት ብቻውን የሚቋቋማቸው ባለመሆናቸው ኢንተርፕራይዞቹንም ሆነ ቴክኒክና ሙያ ተቋማቱን ለመደገፍ እንዲሁም ከስደት ተመላሽ ዜጎችን ለማቋቋም ድጋፍ ማድረግ የጀመሩትን አመስግነው፤ ሚኒስቴር መስሪያቤት
አጋር የሆኑ ድርጅቶች ለዚህ እንዲተባበሩ ጠይቀዋል፡፡

በሁለቱም ክልሎች የሚገኙ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ፣ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች እና የቴክኒክና ሙያ ተቋማት በጦርነቱ ምክንያት የደረሰባቸው ጉዳት ከፍተኛ መሆኑን የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼
ምንጭ- (ኢ ፕ ድ)

በ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ገብተው ለሚሰለጥኑ ተማሪዎች የቅበላ መቁረጫ ነጥብ============      ==============የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴ...
29/03/2022

በ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ገብተው ለሚሰለጥኑ ተማሪዎች የቅበላ መቁረጫ ነጥብ
============ ==============
የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር የሁለተኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና ከወሰዱ ተፈታኞች መካከል የስራ ገብያ ፍላጎትን መሰረት በማድረግ በ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ተማሪዎች በተለያዩ የሙያ ደረጃዎች ገብተው እንዲሰለጥኑ ይፋ ያደረገው የቅበላ መቁረጫ ነጥብ እንደሚከተለው ነው----!!

የወራቤ ዩኒቨርሲቲ በመማር ማስተማር፣ ምርምር፣ ማህበረሰብ አገልግሎትና በቴክኖሎጂ ሽግግር  ከተለያዩ ተቋማት ጋር  ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ፡፡የካቲት 29/2014ወራ/የኒ/ው/ህ...
09/03/2022

የወራቤ ዩኒቨርሲቲ በመማር ማስተማር፣ ምርምር፣ ማህበረሰብ አገልግሎትና በቴክኖሎጂ ሽግግር ከተለያዩ ተቋማት ጋር ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ፡፡
የካቲት 29/2014
ወራ/የኒ/ው/ህ/ግ/ዳ/
ዩኒቨርሲቲዉ ስምምነቱን የተፈራረመዉ ከስልጤ ዞን ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና መምሪያ ፣ ከስልጤ ዞን ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ መምሪያና ከወራቤ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር ነዉ፡፡

የመግባቢያ ስምምነቱ ዓላማ ዩኒቨርሲቲው ከተቋማቱ ጋር በምርምር ፣ በስልጠናና ቴክኖሎጂ ሽግግር አብሮ መስራት ሲሆን ለቴክኖሎጂ ሽግግር የቴክኒክ እገዛ ማድረግ ፣ አቅም መገንባት፣ የአከባቢ ጥበቃና የአረንጓዴ ልማት ስራዎች ተቋማቱ በጋራ ለመተግበር ከተስማሙባቸዉ ዘርፎች መካከል ይጠቀሳሉ፡፡

የወራቤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ኢንጂነር ተውፊቅ ጀማል ወደ ማህበረሰቡ የሚደርስ ቴክኖሎጂ በጋራና በቁርጠኝነት በመስራት በቴክኖሎጂ ሽግግር የላቀ ዉጤት ለማስመዝገብ እንሰራለን ብለዋል፡፡

የስልጤ ዞን ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሹክራላ አወልና የወራቤ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ቡላድ ናሙስ ወራቤ ዩኒቨርሲቲ ከተቋማቱ ጋር በመቀናጀት ማህበረሰቡን ለመቀየር እያሰራ ላለዉ ስራ ምስጋና አቅርበው በቀጣይ የመግባቢያ ስምምነቱን ዓላማ ከግብ ለማድረስ በተጠናከረ ሁኔታ መስራት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡

ስልጤ ዞን ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና መምሪያ

Dirección

Alicho
Siltepec
COLLEGE

Notificaciones

Sé el primero en enterarse y déjanos enviarle un correo electrónico cuando KCIC ቃኮኢኮ ⁻ Kawakoto Construction And Industrial College publique noticias y promociones. Su dirección de correo electrónico no se utilizará para ningún otro fin, y puede darse de baja en cualquier momento.

Compartir

Categoría